Quantcast
Channel: ስፖርት | ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) - Latest Ethiopian News Provider
Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

Sport: የአሮጊት ፉትቦል…..የሴት ጨዋታ –ከገነነ መኩሪያ (ሊብሮ)

$
0
0

genene Mekuria
የብሄረዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሰሞኑን በሬድዮ ሲናገር እንደሰማሁት‹‹እኔ የአሮጊት ፉትቦል መጫወት አልፈልግም››አለ፡፡አሰልጣኙ አሁን እየተኬደበት የምትትሮሽ ጨዋታ ይልቅ ልጆቹን መነሻ ባደረገ በኩል እንዲሰራ ሀሳብ ሲቀርብለት ያንን ለመቃወም የተናገረው ነው‹‹እኔ ቶሎ ባለጋራ ሜዳ የሚገባ ቡድን ነው የምፈለወገው ››አሉ፡፡ባለጋራ ሜዳ ቶሎ መግባት ጥሩ ነው ግን በምንድነው ባለጋራ ሜዳ የሚገባው? ፡፡ቶሎ ባለጋራ ሜዳ የሚገባውተጠልዞ ነው በዚህ መንገድ ደግሞ ከእኛና ባለጋራ ማን እንደተሻለ ብዙ ግዜ ታይቷል፡የእኛ ተጨዋቾች በተለይ ከምእራብ አፍሪካ ቡድን ጋር ሚዛን ላይ ተቀምጠው በምንድነው መቋቋም የሚችሉት ቢባል ያለን ነገር በቴክኒክ በኩል ነው፡፡ይሄ ቴክኒክ መገለጫው በመቀባበል ነው፡፡መቀባበሉ ደግሞ በመረዳዳት ባለጋራን ለመቋቋም ያስችላል፡፡ ቶሎ ወደፊት ኳሱ ሲጣል የእኛ ተጨዋች ተሻምቶ ነው የሚያገኘው(ያውም ካገኘ) ኳስ ሲያገኝ የሚረዳው ስለሌለ በግል ይሞክራል፡፡ በግል ደግሞ እነርሱ በፍጥነትም ጉልበት ይበልጡናል ፡፡እንደሚበልጡንም ለረጅም አመት አይተነዋል፡፡ስለዚህ በግል ተገኝቶ በጉልበት ከተበለጥን ኳስ የያዘ ሰው ረዳት ተበጅቶለት እየተቀባበሉ ባለጋራ ሜዳ ቢገቡ ያዋጣል እንጂ አይጎዳም፡፡

መረዳዳቱን(መቀባበሉን)የአሮጊት ፉትቦል ከተባለ የአሮጊት ባልሆነው ፉትቦል አሰልጣኙ መብለጫ መንገድ ሊያሳዩን ይገባል፡፡ከዮሀንስ በፊት የነበሩት አሰልጣኝ ባሪቶ ሀዋሳ በልምምድ ጌም ተጨዋቾቹ ሲቀባበሉ‹‹ እኔ የሴት ፉትቦል አልፈልግም፡፡ ቶሎ ኳሱን ለአጥቂው ወደፊት ጣሉት››ብለው ትእዛዝ ሰጡ ፡፡ቶሎ ለአጥቂው የሚጥልላቸውን ተጨዋች ቀይረው አስገቡ፡፡ እዚህ በሜዳችን ከአልጀርያ ጋር ቶሎ ለአጥቂው እየተጣለ ምን እንደደረሰብን አይተነዋል ፡፡ ቶሎ ለአጥቂው መጣል ‹‹የወንድ›› መቀባል ደግሞ ‹‹የሴት›› ከሆነ እናም በመቀባበሉ የምንበልጥ ከሆነ አዋጪው የሴት የተባለው ነው፡፡ዮሀንስም እንደባሪቶ ቶሎ ባለጋራሜዳ ለመግባት ወደፊት እየጣለ ያለረዳት ለመጫወት መሞከሩ የባሪቶን ነገር ሊደግምልን ነው፡፡ተጫዋቾቹ የሚችሉት ነገር አለ፡፡በሚችሉት ነገር ላይ እንዲጫወቱ መፍቀድ በሜዳ ላይ ብልጫ እንዲይዙ ማደረግ ነው፡፡የልጆቹን መብለጫ ‹‹የአሮጊት ፉትቦል ነው አልፈልግም….የሴት ፉትቦል ነው አልፈቅድም››በሚል ማጣጣሉ የት እንዳረሰን አይተነዋል፡፡ የሚገርመው አሰልጣኞቹ ያዋጣል በሚሉት ነገር ሊያሳዩን አልቻሉም ፡፡አማራጩንም(የአሮጊት፤ የሴት )በሚል ማጣጣል ስያሜ እየሰጡ እነርሱ በሚሰሩት ነገር እየተዋረዱ እዚህ አድርሰውናል፡፡ያሁኑ አሰልጣኝ ለለውጥ አልመጣም፡፡ ሌሌቹ ትተው የሄዱትን የውድቀት አጨዋወት ሊያስቀጥል ነው፡፡

…የሆንስ መረዳዳቱን ወይም ልጆቹ በሚችሉት በሚያውቁት መንገድ መጫወቱን የአሮጊት ፉትቦል ካለ የአሮጊት ባልሆነው ነገር ባለጋራን መብለጥ እንዳልቻለ አይተነዋል ነገም ይሄንኑ ነገር ያሳየናል፡፡የዮሀንስ ስትራቴጄ ደጋግሞ እንዳወራው ቶሎ ባለጋራ ግብ ጋር መድረስ ነው፡፡

እንዴት ነው የሚደረሰው የሚለው ጉዳይ ነው አስቸጋሪ የሆነው፡፡አሁን እንደታየው ግብ ጋር የሚደረሰው(በተለይ ከሜዳ ውጭ) በሚጣል ኳስ ነው፡የሚጣለውን ኳስ አጥቂዎቹ ለማግኘት ይቸገራል፡፡ቢያገኙም ረዳት ስሌሌለ ቶሎ ይነጠቃሉ፡ምክኒያቱም ብቻለ ብቻ ጉልበት ስለሚጠይቅ የእኛዎቹ በጉልበት የመቋቋም ችግር ስላለባቸው እያስረከቡ ይመጣሉ ቶሎ ግብ ጋር እንዲደርስ የተጣለው ኳስ ቶሎ ባለጋራ እጅ ገብቶ እኛ ላይ የጥቃት ጫናው ይጠነክራል፡፡ቶሎ ግብ ጋር ለመድረስ ሲባል እንቅስቃሴው በግል ነው የሚሆነው፡፡ በግል ጉልበት ስለሚጠይቅ አስቸጋሪ መሆኑን ከዮሀንስ የተሻለ ሰው አስረጅ ሊሆን አይችልም፡በ1975 ዮሀነስ ለብሄራዊ ቡድን ተመርጦ ነበር፡፡በዚያን ግዜ የነበሩት ተጫዋቾቻን በፊዚካል አሁን ካሉት በብዙ እጥፍ ይሻላሉ፡፡ እነርሱ እንኳን በዚህ አጨዋወት ሊቋቋሙ አልቻሉም፡፡ በጉልበት በፍጥነትም ቶጎን የነዮሀንስ ቡድን እንዳልቻለ ሁሉ ያሁን ቡድን ከዚህ አጨዋወት ማስወጣትሲገባው እሱ ያልቻለበትን መነገድ ተጨዋቾችን እንዲተገብሩ ማድረግ ተገቢ አይደለም፡፡ እሱም ያውቃል፡፡ቶሎ ቶሎ ባለጋራሜዳ እየጣሉ መግባቱ ለሌሎች አሰልጣኞችም እንዳላዋጣ ታይቷል፡፡ ዮሀንስ ሌሎች አሰልጣኞች አሁን እሱ እየሄደበት ባለው ነገር ውስጥ ተግብረው ወድቀት ውስጥ ገብተው እንደነበር መማር ይገባዋል፡፡ከአሰልጣኞቹ መማር ብቻ ሳይሆን እራሱም በኢንተርናሽናል ፉትቦል ካገኘው ተሞክሮ ትምህርት መወሰድ ነበረበት፡፡በ1975 ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከቶጎ ሲጫወቱ 4ለ2ተሸንፈው ነው የወደቁት፡፡በተለይ ቶጎ በሜዳው 3ለ0 ሲየያሸንፍ ከሜዳ አላስወጣቸውም ፡፡ከተከላካዪቹ አንዱ ዮሀንስ ከግራ በኩል ለአጥቂዎቹ በረጅሙ እየጣለ ነበር የሚሰጣቸው (ቶሎ እዲያገቡ) እሱ የሚጠልዛቸው ኳሶች በርግጥ ባለጋራ ሜዳ ደርሰዋል ግን የእኛ አልነበሩም፡፡ ዮሀንስ ወደ ባለጋራ ግብ ያሻገራቸው ኳሶች ቶጎ በር ላይ ደርሰዋል ነገር ግን ቶጎ እነዚህን ኳሶች እየተቀበለ በማጥቃት እኛ ላይ ብዙ ጫና ፈጥረውብን 3ለ0 ተሸነፍን፡፡ቶጎ በጣም ነው የበለጠን፡የተበለጥነው እኛ ይዘንለት የገባነው ነገር ለእነርሱ ስለተመቸ ነው፡ በዚያ አጨዋወት ብሄራዊ ቡድኑ ባለጋራን መግጠሙ አዋጪ እንዳልሆነ ይልቅ አክሳሪ እንደሆነ ራሱ ተጫውቶ አይቶታል፡፡፡እሱ ተጫውቶ ያላዋጣውን ነገር ያሁኑ ተጨዋቾች እንዲተገብሩ ማድረጉ ጉዳት ነው፡፡ ያ ቡድን ከቶጎ በፊት ሞሪሸስን ገጥሞ ነው ያለፈው ሞሪሸስን ሲያሸንፉ አጨዋወቱ ትክክል ነው ብለው አመኑ፡፡ ቶጎ ላይ ሞሪሸስ የሰጣቸውን ክፈተት ማግኘት አልቻሉም(ልክ አሁን ብሩንዲን ሲያሸንፉ ትክክል እንደመሰላቸው) ቶጎ በፍጥነት አና ጉልበት ከሞሪሸስ የተለየ በመሆኑ አልቻሉትም፡፡ ይሄ ከሆነ 33 አመት ሆነው ፡፡ዮሀንስ 33 አመት ሙሉ አልተማረም ፤አልገባውም፡፡ቢገባው ኖሮ እኔ ብሄራዊ ቡድን በነበርኩበት ግዜ በሀይል አጨዋወት ስላስቸገሩን በዚህ መንገድ አስቸጋሪ ስለሆነ አሁን በአሰልጣኝነት ግዜ ይሄን መንገድ መቀየር አለብኝ ማለት ሲገባቸው ተመልሰው ባልተቻለበት መንገድ መግባቱ አስገራሚ ነው፡፡በዚያ ላይ በተክለሰውነት የነ ዮሀንስ ቡድን ካሁኑ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች በእጅጉ የገዘፉና ጠንካራ ናቸው ግን እነርሱም(የነዮሀነስ ብሄራዊ ቡድን) በዚያ ሰውነታቸው መብለጥና መቋቋም አልቻሉም(የሰውነት አቀማቸውን ለማነጻጸር እንዲመቻችሁ ያሁን ብሄራዊ ቡድን እና ቶጎን በ1975 የገጠመውን ቡድን ፎቶ አቀርቤላችኋለሁ ፡፡ዮሀንስ ከቆሙት ከግራ ሁለተኛው ነው )እናም ዮሀንስ ተጫውቶ ያልቻለበትን ነገር እንዴት ያሁኑ ትወልድ ሊተገብረው ይችላል፡፡

…………አሁን ይሄ ቡድን በዚህ አጨዋወት ለአፍሪካ ዋንጫ በሆነ ምኪኒያት ቢያልፍ የሚቋቋም ይመስላችኋል?፡፡ ብናልፍም እንኳን ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ሳይሆን አልፈን ምንድነው የምንሰራው?የሚለው ነው መታየት ያለበት፡፡ባለፈው አፍሪካ ዋንጫ የገባው ቡድን አንድ አግብቶ ሰባት ገብቶበት ውራ ሆኖ መጣ ፡፡ጥሩ ነው የተባለለነት ነገር ቀጣይነት አልነበረውም፡፡ጀግና የተባለው ቡድናችን ገብቶ ውራ ሲሆን ጀግንነታቸችን ለውራ ከሆነ ምን ያደርግልናል፡፡በዚያ የአፍሪካ ዋንጫ የውጭ ጋዜጠኖች የእኛን ቡድን ኳስ ጥሩ ናቸው አሉን፡፡ ግን ኳስ የሚጫወት ቡድን ሰርተን አይደለም የገባነው፡፡ በተፈጥሮ ያለን ነገር ይሄ በመሆኑ በዚህ የተወሰኑ ልጆች በግል የሆነ ነገር ስላሳዩ ኳስ ጥሩ ናችሁ አሉን፡፡ታዲያ ለምን ጥሩ ናችሁ የተባልንበትን ነገር(አሁን የአሮጊት የተባለውን) በስልጠና ብናሳድግ እንጠቀማለን፡፡ጋዜጠኞቹ የእኛን ቡድን በጉልበት ጥሩ ናችሁ አላሉንም፡፡ በንጽርር ከሌሎች ቡድን ጋር አስተያይተውን እንደማንበልጥ ስላዩን በጉልበት ጥሩ ናችሁ አላሉም ፡፡እኛ ግን አሁን እየሰራን ያለነው በጉልበት ነው፡፡ይሄ ደግሞ አዋጪ እንዳልሆነ ነው ለብዙ ግዜ የታየው፡፡ዮሀነስ እስካሁን አለቆቻችን የሆኑትን ምእራብና ሰሜን አፍሪካ ቡድኖችን አላገኘም፡በርግጥ ደደቢትን ይዞ የናጀርያን ቡድን ገጥሞ ተበልጦ ነው ከውድድር የወጣው እዚያ 2ለ0 ሲሸነፍ ከነብልጫው ነው፡፡ከዚህ ጨዋታ እንኳን መማር አልቻለም፡፡(በቅርቡ ካደረገው)ከምእራብ ቡድኖች ጋር ወደ ፊት ቶሎ ቶሎ የጣሉ ባለጋራ ሜዳ መግባት እንዳላዋጣ ተጫውቶም አሰልጥኖም ካየው ሌላ አማራጭ መፈለግ ነበረበት ፡፡ግን አማራጩና ጠቃሚውን የአሮጊት ፉትቦል ካለ ከእነርሱ ጋር ሲገናኝ ዳግም አሰቃቂ ነገር ነው የሚታው፡፡ያን ግዜ ሰበብ ደርድሮ ቆይታን ለማስቀጠል ካልሆነ ለውጥ ከእዚህ ቡድን ምንም አይጠበቅም ፡፡
የምእራብ አፍሪካ ቡድኖች የበለጡን በጉልበት ነው፡፡፡እነርሱ በዚህ አጨዋወት የበለጡን እኛም በጉልበት ስለገባን ነው፡፡በዚህ እንቅስቃሴ ለረጅም አመት እየበለጡን ነው፡፡ዛሬም ለረጅም አመት የተበለጥንበትን ነገር አንለቅም ብለን የለውጡን መንገድ‹‹የአሮጊት ነው››በሚል በነበረበት(በተዋረድንበት) ለመቀጠል መዘጋጀት አስገራሚ ነው፡፡መቼ ነው ታዲያ ማመዛዘን የሚችል አሰልጣኝ የምናገኘው? ያስብላል፡፡ ግን ለማመዛዘን የቸገራቸው ምንድነው፡፡ልጆቹ ያላቸው ችሎታ የታወቀ ነው ፡፡ያንን በስልጠና አዳብሮ በሚችሉት መንገድ እንዲጫወቱ ቢደረግ የተሻለ ነው፡፡አሁን ግን በማይችሉበት መንገድ እንዲጫወቱ ተደርገው በዚያ ላይ ተጠያቂ መደረጋቸው ጉዳት ነው ፡፡
– የሚሰጡት ስልጠና ጨዋታን የሚወከል አይደለም፡፡ ስልጠናው በረኛ ይለጋል፤ ሲለጋል ተሻምታችሁ አግኙ ነው፡፡ማሻማት ማሰልጠን አይደለም ይሄን ማን ያቅተዋል?…..መለጋት፤መልስ ምት፤እጅ ውርወራ፤ኮርና፤ክሮስ እነዚህ ሁሉ ማሻማት ናቸው፡፡ በማሻማት ወስጥ ከእኛ ይልቅ የውጭ ቡድናች ተጠቃሚ ናቸው፡፡ከማሻማት ውጭ ያለው ነገር ኳስ ይዞ ተረራድቶ መጫወት እውቀት ነው፡፡ በእወቀት ማሰልጠን ብልህነት ነው፡፡ግን በእወቀት ማሰልጠን አስቸጋሪ ሲሆንባቸው ባለጋራ ሜዳ እየጠለዙ በመግባት ነው የመረጡት፡፡በእወቀት ማሰልጠንና መጫወትን ግን ‹‹የአሮጊት›› ይሉታል
–እነርሱ በመረጡት አጨዋወት መቋቋም እንዳማይችሉ አሰልጣኞቹም ያውቃሉ፡፡ባለጋራን መብለጥ የምንችልበት አጨዋወት ፈልጎ መተግበር ሳይሆን እንዴት ሰበብ እየፈለጉ መቆየት ሚችሉበትን ነገር ነው የሚያስቡት

እከዛሬ የሰሩት አሰልጣኞች እግር ኳሱን ለመለወጥ ሳይሆን ደሞዝ በልተው የሚሄዱ ብቻ ነው ያየነው፡፡ያሁኑም አሰልጣኝ እንደበፊቶቹ በእግር ኳሱ ላይ የምንናፍቀውን ለውጥ የሚያሳየን እንዳልሆነነ ከአየያዙ መረዳት ይቻላል

– አሰልጣኞች ያመኑበትንና ያወጣል ያሉትን አጫወወት ሀላፊነት ሲወስዱ አይታዩም፡፡ይሄነገር ያወጣናል ካሉ በዚህ ለሚመጣው ነገር ሀላፊነት ወስደው ሲሸነፍም እኔ ነኝ የምጠየቀው ብለው መናገር አለባቸው፡፡ይሄ ማለት የመረጡት ነገር ስህተት ከሆነ ወደ ተሻለና ወደሚያዋጣ ነገር እንዲመጡ ያደርጋል፡፡አሁንግን ሀላፊነት ስላማይወሰዱ ከተሳሳተው ነገር መውጣት አይችሉም፡፡ስለማይወጡም በተሸነፉ ቁጥር ሰበብ እየደረደሩ የሚፈለገው ለውጥ ሊመጣ አልቻለም፡፡

– – አንዳንዴ ቡድኑ ሲያሸንፍ አሰልጣኞቹ ያሸነፉበትን መንገድ እንኳን አያውቁም፡፡እንዴት እንዳሸነፈ ስለማያውቁ ሲሸነፍ ሰበብ ይደረድራሉ፡፡ያሸነፈበትን ነገር ካላወቁ ሲሸነፍ ስህተቱ የቱ ጋር እንዳለ አይረዱም፡፡ለዚህም ነው ከማስተካከል ይልቅ ሰበብ የሚደረድሩት፡፡ለአፍሪካ ዋንጫ የገባው ቡድን ባለጋራውን(እነ ቡርኪናን) መቋቋም ያቃተው ማጣሪያውን ሲያልፍ እንዴት እንዳሸነፈ ስለማያውቅ ነው፡፡ውጤት የሚባለው አንድ ጨዋታ አሸንፎ መፎለል ሳይሆን ቀጣይነት ባለው መንገድ ብልጫ ይዞ ማሸነፍ የሚችል ቡድን ሲገኝ ነው፡ትናንትም ዛሬም ቀየጣይነት ያለው ነገር ይዞ የሚሄድ ቡድን አላገኘንም፡፡ቀጣይነት ያለው ሰበብ ብቻ ነው ከአሰልጣኞቹ ያገኘነው፡፡አሰልጣኙ ባመኑበት፤ ያዋጣል ብሎ በመረጠው ነገር ለውጥ ካላመጣ በአማራጩ ሀሳብ መሞከር አለበት
– እኛ ሀገር ለውጥ እንዲመጣ ሚዲያው ትልቅ ስራ መስራት አለበ ፡፡ከማሸነፍና መሸነፍ ውጭ በእወቀት ቢዘግቡ አሰልጣኞችን ወደ እውነተኛው ነገር ሊያመጧቸው ይችላሉ፡፡ቡድኑ ሲያሸንፍ ጉሮ ወሸባ ይላሉ፡፡ያሸነፈበትን ነገር መነሻችን ነው ወይ ብለው አየይመረምሩም ፡ብሩንዲን ያሸነፍንበት የጨዋታ እንቅስቃሴ ሌሎች ቡድኖች ለረጅም አመት ሲጨፈጭፉን የነረበት እንቅስቃሴ መሆኑ ታውቆ ከጉሮ ወሸባዬ ነገር ወጥተን ይሄ ነገር ከሌሎች ጋር አላዋጣንም(ከሰሜንና ምእራቡ) ብሩንዲው ውጤት አሳሳች ነው ቢሉ አሰልጣኞችም ወደ ትክክለኛው ነገር ሊመጡ ይችላሉ፡፡ለወደፊቱ ይሄ ቢስተካከል አሰልጣኞቹን ማረም ይቻላል ፡፡

ያሁኑ አሰልጣኝ በቅርብ ከሀላፊነት ይነሳል፡፡ግን አሰልጣኙን በምን እናስታውሰዋለን፡፡ምኪኒያቱም ምንም የሰራልንና ያስቀመጠልን ነገር የለም፡፡ሌሎች አሰልጣኞች ያልቻሉበትን መንገድ እያስቀጠለ ነው፡፡በአምስተኛው አፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን ያሳለፉት አሰልጣኝ ሽፈራው በሴኔጋል 5ለ1 በቱኒዝያ 4ለ0 ተሸንፈው ከምድቡ ከአጠቃላይም ውራ ሆነው ተመለሱ፡፡ ለሰባተኛውም ያሳለፉት አሰልጣኝ በአይቮሪኮስት 6ለ1 በሱዳን 3ለ0 ተሸንፈው ከምድቡም ከአጠቃላዩም ውራ ነው የወጡት፡፡መንግስቱ ወርቁ ለ13ተኛው አፍሪካ ዋንጫ ቡድኑ እንዲያልፍ አደረገ፡፡ ነገር ግን አንድም ጨወታ ሳያሸንፍ ቡድኑ በሶስቱም ጨዋታተበልጦ ከምድቡም ከአጠቃላዩም ውራ ነው የወጣው(ከስምንት ቡድን ስምንተኛ) ከሊቢያወው ቀጥሎ በ29ነኛ አፍሪካ ዋንጫ በ2005 አለፍን በማለፋችን እግር ኳሱ እንደተለወጠ ተወራ፡፡ይሄኛውም እንደሌሎቹ ከምድቡም ከአጠቃላዩም ውራ ነው የወጣው፡፡ባለጋራን መብለጥ ቀርቶ መቋቋም አልቻለም አንድ ግብ አስቆጥሮ ሰባት ገብቶበት ነው የተመለው፡፡እነዚህን ለአፍሪካ ዋንጫ ያሳለፉትን አሰልጣኞች በምን አንስታውሳቸው ምክኒያቱም ምንም ያስቀመጡልን ነገር የለም፡፡ የምእራብ አፍሪካን ቡድኖች መቋቋም አቅቷቸው ነው የወጡት፡፡እነዚህን አሰልጣኞች የማናስታውሳቸው እኛ በምንበልጥበት ሳይሆን በተበለጥንበት ይዘውን ስለገቡና ስላስጨፈጨፉን ነው፡፡እነዚህ ለአፍሪካ ዋንጫ አሳልፈው ምንም ሳይሰሩ ውራ ወጥተው ተበልጠው የተረሱ ናቸው፡፡ ሌሎች አሰልጣኞችም ምንም ሳያሳዩን ከሀላፊነት ተነስተዋል የሆንስም ከእነኚህ አንዱ ነው ምንም ሳያሳየን ወደ ለውጥ ሳይወስደን ችግሩን ሳይፈታ ከሀላፊነት ይነሳል እናም በዚው ይረሳል፡፡ከሌሎች አሰልጣኞች ይልቅ በአሁን ሰዓት የካሳዬ ስም የሚነሳው ትንሽ የለውጥ መንገድ ስላሳየና ስላስቀመጠ ነው፡፡ለሌሎች ከተከተሉበት መንገድ ወጣ ስላለ ነው፡፡ፍንጭ ለማሳየት በመሞከሩ ነው፡፡ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ በራሱ ምንም ነገር የለውም….ማለፉችን ከእድገት ጋር ቢሆን ከለውጥ ጋር ቢሆን ጥሩ ነው፡፡፡ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፋችን እድገታችንን ሳይሆን ውድቀታችንን ነው የሚየሳየው(በብዙ ግብ እየተሸነፍን ውራ ሆነን ስለምንወጣ)፣፡እከዛሬ የታየው ተስፋ የሌለውና በባለጋራ በእቅስቀሴና በውጤት ተበልጠን ነው የታየው፡፡ዛሬም ሀላፊነቱን የያዙት ከሌሎች ሳይማሩ ለሌሎች ያሳዩትን ደካማ ነገር ለመድገም ነው፡፡ገና አንድ ጨዋታ ሲሸነፉ‹‹የኢትየዮጵያ እግር ኳስ ችግር አለው፤አጥቂ የለም፤በረኛ የለም››ይላሉ ሲረከቡ እኮ ይሄን አውቀው ነው ፡፡ሲቀጠሩ ለአፍሪካ ዋንጫ እናሳልፋለን ይሉና ሲሸነፉ የቅድሙን ችግሮች ያነሳሉ
– አንድ ነገር ደግሞ አለ፡፡ወደ ለውጥ የሚወስድ ቡድን መስራት ሲያቅታቸው እንትናን ወደ ብሄራዊ ቡድን ያመጣሁት እኔ ነኝ በሚል ክሬዲት በዚህ እንዲያዝላቸው ይፈልጋሉ፡፡ ኤፌም ኦኔራ በተጋጣሚ ቡድኖች እንደዚያ ተቀጥቅጦና ተበልጦ ከሄደ በኋላ እነ አሉላ፤ ሽመልስ፤ኡመድን ብሄራዊ ቡድን ያመጣኋቸው እኔ ነኝ ብሎ በሰራው ቡድን ሳይሆን በልጆቹ ክሬዲት እንዲያዝለት ሲወተውት ነበር፡፡ባሪቶም ናትናኤልን አንዳርጋቸውን ብሄራዊ ቡድን ያመጣሁት እኔነኝ አሉን፡፡ አሁን ደግሞ ‹‹ራምኬሎን ብሄራዊ ቡድን ያመጣሁት እኔ ነኝ››በሚል እየተወተወትን ነው …አኛ እንትናን ማምጣታቸው ሳይሆን ባለጋራን መቋቋም የሚችል ተስፋ ያለውና የምንመካበት ቡድን ሲሰሩልን ነው፡፡ካለበለዚያ እገሌን ብሄራዊ ቡድን ያመጣሁት እኔ ነኝ በሚል የለጥው ቡድን ሳይሰሩልን ቢቆዩ ፋይዳ የለውም፡፡የእኔ ከእከሌ አሰልጣኝ ይለያል ለማለት ነው፡፡በአንድ ወቅት በሴኔጋል 3ለ0የተሸነፈው ቡድን አሰልጣኝ ‹‹የእኔ ቡድን ጥሩ ነው፡፡ያለፈው አሰልጣኝ 4ለ0 ነው የተሸነፈው፡፡ እኛ እንደነርሱ በዙ አልገባብንም›› በሚል የእሳቸው ቡድን በምን ከሌሎች እንደሚለይ ነግረውን ነበር ፡፡4ለ0 የተሸነፈው 3ለ0 የጠጣውም በተመሳሳይ እንቀሰስቃሴ ተበልጠው ምን የተሻሻለ ነገር ሳያስቀምጡልን ነው የሄዱት፡፡
– ያሁኑም አሰልጣኝ ደሞዝ ተቀብሎ ለመሄድ ሳይሆን ለለውጥ ቢሰራ አይረሳም፡፡

The post Sport: የአሮጊት ፉትቦል…..የሴት ጨዋታ – ከገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) appeared first on Zehabesha Amharic.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

Trending Articles