ከዓመታት የማጣሪያ ውድድሮች በኋላ በሩሲያ አስተናጋጅነት የሚካሄደው በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀው የ2018 የዓለማችን ታላቁ የእግር ኳስ መድረክ ሊጀመር የወራት ዕድሜ ቀርቶታል። ከወዲሁም ያልተጠበቁ ክስተቶችን ማመልከት ጀምሯል። በፍልሚያው ሜዳ የተጠበቁት ሲቀሩ፤ ያልተጠበቁት የተሳትፎ ትኬት ቆርጠዋል። የመድረኩ ድምቀቶች ብርቱካናማዎቹ ሆላንዶች እና ጣሊያኖች በአይስላንድ እና በፓናማ ተተክተዋል። በመድረኩ በአምስት አገራት የምትወከለው አህጉራችን አፍሪካም ብትሆን አብዛኞቹን ተወካዮቿን ቀይራለች። […]
↧