ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ላይ በትግራይ ስታድየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ ፋሲል ወልዋሎን 1ለ0 አሸንፏል፡፡ ለፋሲል የማሸነፊያ ግቧን 57ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ያሬድ ባየህ ነው፡፡ ፋሲል ከነማ ባለፈው እሁድም ሆነ ዛሬ በመቀሌ ያደረገው ጨዋታ በሰላም ተጠናቋል:: በስታዲየሙ የተገኙ የትግራይ ክለብ ደጋፊዎች ፋሲል ከነማም ኳስ ሲይዝ ሲያበረታቱ እንደነበር ከስፍራው የሚመጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ::
↧