በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታዎች ዛሬ በተለያዩ ከተሞች ተደርገዋል:: በውጤቱም: መቐለ 70 እ. ፋሲል ከነማን 1ለ0 ሲያሸንፍ ጅማ አባ ጅፋር እና ድሬዳዋ ከተማ 3-3 ሲለያዩ ባህር ዳር ከተማ ስሑል ሽረን 2ለ0 አሸንፏል:: በትናንትናው ዕለት በተደረጉ ጨዋታዎች አዳማ ከተማ 0-0 ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲለያዩ ደደቢት በሜዳውና በደጋፊው ፊት በመከላከያ 3ለ0 ተሸንፏል:: በአዲስ አበባ የተደረገው ወላይታ ድቻ እና ሲዳማ ቡና ጨዋታ ሲዳማዎች 2ለ1 አሸንፈዋል::
The post በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታዎች ዛሬ በተለያዩ ከተሞች ተደርገዋል appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.