የብሄራዊ ቡድናችን ጎል ለአዳኝ ሳላዲን ሰዒድ ኢትዮጵያ ከአልጄሪያ ጋር ለምታደርገው ወሳኝ ጨዋታ በአሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ ጥሪ ቢደረግለትም መጫወት እንደማይችል ሪፖርት አደረገ:: በዚህም የተነሳ ከብሄራዊ ቡድኑ ውጭ መሆኑ ተሰማ::
ከዚህ በፊት በነበሩ የብሄራዊ ቡድን ጨዋታ ከጉዳት ካገገመ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች ከምርጫ በመዘለሉ ምክንያት ከብሄራዊ ቡድን ርቆ በመቆየቱ እንዳኮረፈ የሚነገርለት ሳላዲን ሰዒድ ኢትዮጵያ ከአልጄሪያ ጋር ለምታደርጋቸው ጨዋታዎች በአሰልጣኙ ጥሪ ቢደረግለትም እንደማይጫወት ገልጿል;;
በተያዘው የውድድር አመት በቂ ጨዋታዎችን ማድረግ ባለመቻሉ በአእምሮ እና በአካል ረገድ ለጨዋታ ያለው ዝግጁነት ብቁ ደረጃ ላይ እንደማይገኝ ገልጿል የተባለው ሳልሃዲን ብሄራዊ ቡድኑ ከአልጄሪያ ጋር በሚኖረው ጨዋታ ላይ መሰለፍ እንደማይችል ለአሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ በማሳወቅ ከብሄራዊ ቡድኑ ውጪ ሆኗል፡፡
ሳልሃዲን በኢትዮጵያ እግር ኳስ አፍቃሪያን ዘንድ በተለይ ሃገሪቱ ወደ አፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ከረዳት በኋላ “ጥቁር ሰው” እየተባለ በአድናቆት ተዘምሮለታል::
The post Sport: ሳልሃዲን ሰዒድ ብሔራዊ ቡድናችን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ጨዋታ መሰለፍ እንደማይችል አስታወቀ | አኩርፎ ይሆን? appeared first on Zehabesha Amharic.