(ዘ-ሐበሻ) በአፍሪካ ቻምፒዮንስ ሊግ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሻምፒዮናው ውጭ መሆኑን ዛሬ አረጋገጠ::
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፈው ሳምንት ባህር ዳር ላይ በተደረገ ጨዋታ ከኮንጎ ዲሞክራቲኩ ማዜምቤ ክለብ ጋር በ2ለ2 አቻ ውጤት የተለያየ ቢሆንም በዛሬው የመልስ ጨዋታ ግን የማዜምቤ ክለብ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ደቂቃዎች ሲቀራቸው ባገኙት ፍጹም ቅጣት ምት የተነሳ ከውድድሩ ውጭ ሆነዋል:: ለኮንጎው ቡድን ጆናታን ቦሊንጊ ፍፁም ቅጣትምቷን ወደ ግብነት በመቀየሩ ነው በድምር ውጤት 3 ለ 2 ቅዱስ ጊዮርጊስ ተሸንፎ ከቻፒዮናው ውጭ ሆኗል::
ዛሬ በተደረገ በሌላ የአፍሪካ ቻምፕዮንስ ሊግ ጨዋታ የሞዛምቢኩ ፌሮቫሪዮ ማፑቶ እና የዲሞክራቲክ ኮንጎው አስ ቭስታ ክለብ 1ለ1 ተለያይተዋል::
The post ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአፍሪካ ቻምፕዮንስ ሊግ ውጭ ሆነ appeared first on Zehabesha Amharic.