(ዘ-ሐበሻ) ከደቂዎች በፊት በዳይመንድ ሊግ ውድድር በኳታሯ ዶሃ ከተማ በተደረገው ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አልማዝ አያና በ3ሺ ሜትር የሴቶች ውድድር አንደኛ በመውጣት አሸነፈች::
አልማዝ ውድድሩን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 8 ደቂቃ ከ23.1 ሰከንድ መሆኑ ታውቋል:: በዚሁ በዳይመንድ ሊግ ውድድር ኬንያዊቴ ሜርሲ ቸሮኖ 2ኛ ስትወጣ ውድድሩን በ8:26.36 ጨርሳለች:: በዚህ ውድድር 3ኛ የወጣችው ገለቴ ቡርቃ ስትሆን ውድድሩን በ8:28.49 ጨርሳለች::
ከ4ኛ እስከ 6ኛ ያለውን ቦታ የያዙት ኬንያውያኑ አትሌቶች ሲሆኑ እቴንሽ ዲሮ ነዳ 7ኛ ሆናለች:;
እንኳን ደስ አለን::