Image may be NSFW.
Clik here to view.
ስሜነህ ታደሰ | ለዘ-ሐበሻ ስፖርት
(ዘ-ሐበሻ) ስፔናዊውን ሚካኤል አርቴታን ያጣው አርሰናል ስዊዘርላንድዊውን የመሐል ተጫዋች በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረሙን አስታወቀ::
አርሰናል ስዊዘርላንዳዊው ግራኒት ሳካን ከቦርሲያ ሞንቼግላባ ያስመጣው ከ35 ሚልዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ በተጨማሪ በሳምንት 110ሺህ ፓውንድ ደመወዝ ለመክፈልም በመስማማት ነው::
“ለረዥም ጊዜ ስናልመው የነበረውን ተጫዋች አግኝተናል” ያሉት የአርሰናሉ አለቃ አርሴን ዌንገር ለረዥም ጊዜ ተጫዋቹን ወደ ኤመሬትስ ስታዲየም ለማምጣት ይሰሩ እንደነበር ተናገረዋል:: የመሀል ሜዳው ተጫዋች የቡንደስሊጋ እና የቻምፒዮንስ ሊግ ልምድ እንዳለው ያወሱት ዌንገር የ23 ዓመቱን ስዊዘርላንዳዊ ክለባቸውን በሚቀጥለው ሲዝን እንደሚያጠናክረው ያላቸውን ዕምነት ገልጸዋል::
በባሴል ከ2010 – 2012 የተጫወተው ሳካ 67 ጊዜ ተሰልፎ 3 ጎሎቾን አስገብቷል:: እንዲሁም ለቦርሲያ ሞንቼግላባህ ከ2012 እስከ 2016 ለ134 ጨዋታዎችን አድርጎ 9 ጎሎችን አግብቷል:: ለ41 ጊዜያት ያህል ለስዊዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን የተጫወተው ሻካ 6 ጎሎችን አስቆጥሯል::