ቦጋለ አበበ የዓለም የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ቻምፒዮኗ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ከረጅም ጊዜ በኋላ ወደ ውድድር እንደምትመለስ ታውቋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በድህረ ገፁ እንዳስንበበው ገንዘቤ በቀጣዩ የፈረንጆች ወር መጀመሪያ ወደ ውድድር ተመልሳ የቤት ውስጥ የዙር ውድድር መጀመሪያ በሆነው በጀርመን ካልሹር ተሳታፊ ትሆናለች። ገንዘቤ እኤአ በ2014 በዚሁ ስፍራ ተወዳድራ የዓለም የቤት ውስጥ የአንድ […]
↧
ጀግናዋ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ወደ ውድድር ልትመለስ ነው
↧
ሮቤል ኪሮስ የቀድሞው ዋናተኛ የአሁኑ ስደተኛ |በቪዲዮና በጽሑፍ የቀረበ
በሪዮ አሎምፒክ ኢትዮጵያን መሳለቂያ ያደረገው ሮቤል ኪሮስ በአሜሪካ ስደት ጠይቋል። ልጁ ወደ አሜሪካ ከመሄዱ በፊት በኤፍ ኤም ፣ ከሰይፉ ፋንታሁን ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ አንድ የአሜሪካ “ፕሮፌሽናል ክለብ” በኮንትራት እንደወሰደው ተናግሮ ነበር። የሹክሹክታ ምንጮች እንደሚሉት፣ ልጁ የውሃ ዋና ክለብ አላገኘም። በአሜሪካ የስራ ኮንትራትም አልተፈራረመም። እንደማንኛውም የህወሃት ባለስልጣናት ልጅ ወደ አሜሪካ ተልኳል። ለግሪን ካርዱ […]
↧
↧
ጥሩነሽ ዲባባ በለንደን ማራቶን እንደምትሳተፍ አስታወቀች
(ዘ-ሐበሻ) ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በለንደኑ ማራቶን እንደምትሳተፍ ዛሬ በትዊተር ገጿ ላይ አስታወቀች:: “በመጪው ኤፕሪል ወር በሚደረገው የለንደን ማራቶን ላይ እንደምሳተፍ ስገልጽ በደስታ ነው” ስትል ጥሩነሽ በአጭሩ ተሳትፎዋን ገልጻለች:: The 2018 Virgin Money #LondonMarathon የሚሰኘው ይኸው ውድድር እሁድ ኤፕሪል 22, 2018 እንደሚደረግ ከወጣለት መርሀ ግብር ለመረዳት ተችሏል:: ጥሩነሽ ዲባባ ቀነኔ የተወለደችው፤ ከአባትዋ ከአቶ ዲባባ ቀነኔ […]
↧
በአዲስ አበባ ሊካሄድ የነበረው የሽረ እንዳስላሴ እና ባህርዳር ከተማ ጨዋታ ተጫዋቾቹም፣ ተመልካቹም፣ ዳኛውም ሜዳው ውስጥ ከገቡ በኋላ እንዲቆም ተደረገ
(ሶከር ኢትዮጵያ) በኢትዮዽያ ከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ 11ኛ ሳምንት ሽረ ላይ መካሄድ የነበረበት የሽረ እንዳስላሴ እና ባህርዳር ከተማ ጨዋታ በፌዴሬሽኑ ሊግ ኮሚቴ ውሳኔ መሰረት ባለፈው እሁድ ጥር 20 ለገጣፎ ላይ በ08:00 ላይ ሊደረግ መርሀ ግብር ቢወጣለትም የፀጥታ አካላት በበቂ ሁኔታ ባለመኖሩ በሚል ምክንያት ለዛሬ ማክሰኞ ተላልፎ እንደነበር ይታወሳል። ይኸው ውድድር ታዲያ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 22/2010 […]
↧
ገንዘቤ ዲባባ 1500 ሜትር ፈጣኑን ሰአት አስመዝግባ ድሏን ድርብ ስታደርግ ፤ ሀጎስ ገ/ ህይወት በቀደሚነት አሸንፏል
በምዕራባዊቷ የጀርመን ካርልሱር ከተማ ላይ ምሽቱን በተካሄደው የIAAF World Indoor Tour 2018 ውድድር በ1500ሜትር ርቀት አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ከታናሽ እህቷ አና ዲባባ ጋር በውድድሩን ተካፍለው ገንዘቤ ውድድሩን በ1ኛነት ከማሸነፏም በተጨማሪ በ1500 ሜትር እስከዛሬ ከተመዘገበው ውጤት እጅግ ፈጣኑን ሰአት 3:57:45 በመግባት አዲስ ታሪክ አስመዝግባለች። በዚህ ውድድር ላይ የተካፈለችው የገንዘቤ ታናሽ እህት አና ዲባባ በ10ኛነት መጨረሻ ሆና […]
↧
↧
ከስታዲየም ወደ ቤተመንግስት
ብሩክ በርሄ ለዓመታት በእግር ላይ ጎል በማስቆጠር የአለም ኮከብነት ማዕረግን ተጎናፅፏል፡፡ እግር ኳስን በሚገባ አጣጥሟል፡፡ እስከ ዛሬ ካስቆጠራቸው ጎሎች የተለየውን ግብ ደግሞ በቅርቡ በማስቆጠር የዓመታት ህልሙን እውን አድርጓል፡፡ ብቸኛው አፍሪካዊ የፊፋ ባለንዶር ባለ ክብር ጆርጅ ዊሃ፡፡ ዊሃ ፖለቲካውን ከተቀላቀለ ቢከራርምም፤ አዲሱ የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በመሆን ቃለ መሃላ የፈፀመው ከሳምንት በፊት ነበር፡፡ በሞንሮቪያ ስታዲየም በተካሄደው ቃለ መሃላ […]
↧
ሱፐር ቦል 52 –በኢግልስ አሸናፊነት ተጠናቋል –አስገራሚነቱ ግን ያ ብቻ አይደለም
(አድማስ ስፖርት) ሦስት ጊዜ ለሱፐር ቦል መቅረብ የቻለው ኢግልስ ለመጀመሪያ ጊዜ 41-33 አሸንፏል። በሱፐር ቦል ታሪክ 33 ነጥብ አስቆጥሮ በመሸነፍ ደግሞ ፓትርየትስ ታሪክ ሰርቷል። 6ኛውን ሱፐር ቦል በመውሰድ ታሪክ ለመስራት የቋመጠው ቶም ብሬዲ አልተሳካለትም። ጨዋታው ሊጠናቀቅ 3 ደቂቃ ሲቀር የኢግልሱ ዛክ ኢርትዝ ያገኛት ተች ዳውን ነፍስ የዘራች ነበረች፣ ከሷ በላይ ደግሞ ብራንደን ግራሃም የቶም ብሬዲን […]
↧
ገንዘቤ ዲባባ ብሔራዊ ቡድኑን ትመራለች
ብርሃን ፈይሳ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሊጀመር ቀናት ብቻ የሚቀሩት ሲሆን፤ ሀገራትም ብሔራዊ ቡድኖቻቸውን በማሳወቅ ላይ ይገኛሉ። በተለያዩ ርቀቶች ውድድሩ ላይ ተሳታፊ የሚሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም በአትሌት ገንዘቤ ዲባባ እየተመራ በርኒንግሃም ላይ እንደሚገኝ፤ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር አስታውቋል። 17ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በእንግሊዟ በርኒንግሃም የዛሬ ሳምንት የሚጀመር ይሆናል። ለአራት ቀናት በሚቆየው […]
↧
ንግስቲቱ 5ተኛውን ወርቅ አጠለቀች
(ኢትዮ-ኪክ) የአለም የቤት ውስጥ ውድድሮች ንግስት ገንዘቤ ዲባባ በእንግሊዝ በበርኒገሀም እየተካሄደ በሚገኘው የአለም የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና በቀናት ልዮነት ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ለሀገሯ አስገኝታለች። ገንዘቤ የ1500 ሜትር ርቀቱን በ4:05.27 በመግባት ከማሸነፏ በተጨማሪም በአለም የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ያገኘቻቸውን የወርቆች ቁጥር 5 አድርሳለች።
↧
↧
እንግሊዝ ራሷን ከሩሲያው የዓለም ዋንጫ የምታገል ከሆነም በፊፋ ደንብ መሰረት በ2022 የኳታር ዓለም ዋንጫ እንዳትሳተፍ ትታገዳለች
ብርሃን ፈይሳ ሩሲያ ከምዕራባዊያኑ ሃገራት ጋር ለረጅም ጊዜ ሆድ እና ጀርባ ሆና መቆየቷ ይታወቃል። በቅርቡ ግን በተለይ እንግሊዝ እና ሩሲያ ፖለቲካዊ ውጥረት ውስጥ የገቡ ሃገራት ሆነዋል። በዚህ ምክንያትም እንግሊዝ በተያዘው የፈረንጆቹ ዓመት መጨረሻ በሩሲያ አዘጋጅነት ከሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ብሄራዊ ቡድኗን ልታገል ትችላለች የሚል ስጋት ተፈጥሯል። የዓለምን እግር ኳስ ተቆጣጣሪው(ፊፋ) በበኩሉ እንግሊዝ በዓለም ዋንጫው የማትሳተፍ ከሆነ […]
↧
ወላይታ ዲቻ ተሸለመ
(ዘ-ሐበሻ) ባለፈው እሁድ የግብጹን ዛማሌክ ክለብ ካይሮ ላይ በሜዳውና በደጋፊው ፊት ያሸነው የወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ ወደ ሃገሩ ሲመለስ ሽልማት ተበረከተለት:: ከካይሮ አዲስ አበባ ማክሰኞ ምሽት የገባው የወላይታ ዲቻ ክለብ በቀጣይ ዙር ከታንዛኒያው ያንግ አፍሪካንስ ይጫወታል:: ታሪካዊ ድል ያስመዘገበው ወላይታ ዲቻ ትላንት ከሐዋሳ ወደ ሶዶ ሲያመራ በርካታ ቁጥር ያለው ህዝብ አቀባበል ተደርጎለታል:: በተጨማሪም የወላይታ ዞን […]
↧
የወልዲያ ከነማና የሲዳማ ቡና ጨዋታ በአስለቃሽ ጭስ ለ10 ደቂቃዎች እንዲቋረጥ ተደረገ
(ዘ-ሐበሻ) በሜዳው እንዳይጫወት. የተፈረደበት የወልዲያ ከነማ ቡድን በገለልተኛ ሜዳ ሰበታ ላይ ከሲዳማ ቡና ጋር ዛሬ እንዲገናኙ መርሃ ግብር ወጥቶ የነበረ ሲሆን የዛሬው ጨዋታ ደጋፊዎች ባስነሱት ተቃውሞ ለ10 ደቂቃዎች መቋረጡን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ዘገቡ:: እንደምንጮቻችን ዘገባ ወልዲያ ከነማ ያገባቸውን 2 ጎሎች የመስመር ዳኛው በመሻሩ በተፈጠረው የደጋፊ ቁጣ ፖሊስ አከታትሎ በተኮሰው አስለቃሽ ጭስ ጨዋታው ከ86ኛው ደቂቃ ጀምሮ ለ10 […]
↧
Sport: ጋናዊው የ21 ዓመት አጥቂ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ፊርማውን አኖረ
እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር ታህሳስ 7 1996 በጋና ርዕሰ መዲና የተወለደው የ21 ዓመቱ ሪቻርድ አፒያ 1 ሜትር ከ 75 ሴንቲ ሜትር የሚረዝመው የቀኝ እግር አጥቂ ስፍራ ተጫዋቹ ፈረሰኞቹን ከመቀላቀሉ በፊት ፍሪ ኤጀንት የነበረ ቢሆንም ከዛ በፊት በሩቅ ምስራቅ እሲያ ላኦስ ፕሪሚየር ሊግ ለቻምፓሳክ ዩናይትድ እንዲሁም ለቺታ ኤፍ.ሲ ተጫውቷል። እንዲሁም ለጋና ከ20 ዓመት ብሔራዊ ቡድን ተጫውቶ […]
↧
↧
የትግራይ ክለብ መሪ ዳኛ መደብደባቸው አሳፋሪ መሆኑ ተገለጸ
(ቢቢኤን) ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተባለው የእግር ኳስ ክለብ ቡድን መሪ የሆኑ ግለሰብ፣ ዳኛ መደብደባቸው አሳፋሪ ድርጊት እንደሆነ ተገለጸ፡፡ ብዙዎች በተለይም የስፖርት ቤተሰቡ በአሳፋሪነት እና በእብሪተኝነት የፈረጀው ይኸው ድርጊት የተፈጸመው፣ ትላንት ሰኞ በአዲስ አበባ ስታዲዬም በተካሄደ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ላይ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች መርሐ ግብር መሠረት በዕለቱ ወልዋሎ እና መከላከያ ግጥሚያ እያካሄዱ ነበር፡፡ […]
↧
ተደባዳቢው የወልዋሎ ቡድን መሪ በቁጥጥር ስር ውሎ በዋስ ተለቀቀ
አርቢትር ኢያሱ ፈንቴን የደበደበው የወልዋሎው ቡድን መሪ ማሬ ገብረ ጻዲቅ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በዋስ ተለቋል። ከፌዴሬሽኑ ውስጥ አዋቂ በተገኘ መረጃ የጨዋታው ኮሚሽነር በቀረበ ጥያቄና የኮማንድ ፖስት አዋጁን በመተላለፉ ትላንትና ምሽት ለጥያቄ ወደ 3ኛ ፖሏስ ጣቢያ ተወስዶ ቃሉን ከሰጠ በኋላ በዋስ ተለቋል። ክለቡ ወልዋሎ በዲሲፕሊን ቀልድ አላውቅም በሚል ከስራ ያሰናበተው ቢሆንም የዲሲፕሊን ኮሚቴ ጠንካራ […]
↧
የዳኞችና የፌዴሬሽን አመራሮች ስብሰባ በኮማንድ ፖስቱ ተከለከለ * ሚዲያ አይገኝም
የዳኞችና የፌዴሬሽን አመራሮች ስብሰባ በኮማንድ ፖስቱ ተከለከለ:: እሁድ በጁፒተር ሆቴል ሊካሄድ የታሰበው ይኸው ስብሰባ የፍቃድ ጥያቄ ቢቀርብም በኮማንድ ፖስቱ መከልከሉ ታውቋል። ከፌዴሬሽኑ ውስጥ አዋቂ በተገኘ መረጃ ፕሬዝዳንቱ ከመከላከያ ሚኒስቴር ወይም ከፌዴራል ፖሊስ አመራሮች ጋር ተነጋግረው ፍቃድ እንዲገኝ ለማድረግ እየጣሩ መሆናቸው ታውቋል። ምናልባት የአቶ ጁነዲን ጥረት ተሳክቶ ውይይቱ የሚካሄድ ከሆነ ለመገናኛ ብዙሃኑ ዝግ መሆኑ ታውቋል::
↧
ፊፋ አሳውቁኝ ባለ ማግስት ዳኛውን የደበደበው የወልዋሎ ቡድን መሪ አቶ ማሩ ገብረጻድቅ ከማንኛውም የእግር ኳስ እንቅስቃሴ ዕድሜ ልክ ታገደ
ብስራት ራድዮ የዘገበው እንደወረደ: በ22/08/2010 በአዲስ አበባ ስታዲየም ከመከላከያ ጋር በተደረገው የፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ላይ የተፈፀመውን ጥፋት በሚመለከት ከጨዋታ አመራሮች የቀረበን ሪፖርት ተንተርሶ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ኮሚቴ ውሳኔ ማስተላለፉን ብስራት-ስፖርት አረጋግጧል። የእለቱን አርቢትር እያሱ ፈንቴን የመታው የቡድን መሪ አቶ ማሩ ገብረፃድቅ ከማንኛውም የእግር ኳስ እንቅስቃሴ እድሜ ልክ እገዳ ተጥሎበታል። በቡድን መሪው ጥፋት ምክንያት […]
↧
↧
Sport: የ2018ቱ የዓለም ዋንጫ
ዳግም ከበደ የ2018ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ሊጀመር ቀናቶች ቀርተውታል። አምስት ሳምንታት እና 39 ቀናቶች የቀሩት ይህ አጓጊ የዓለማችን ምርጥ የእግር ኳስ ስፖርት በሩሲያ አስተናጋጅነት የሚካሄድ ነው። በአራት ዓመት አንድ ጊዜ ለአንድ ወር በዘለቀ የውድድር ቀናት አጓጊ ትዕይንቶች ይስተዋሉበታል ተብሎ ይጠበቃል። ያልተጠበቁ የእግር ኳስ ውጤቶች፣ ቀልብን የሚስቡ የደጋፊ ትዕይንቶች፣ ለጆሮ ያልተለመዱ፤ ለእይታ እንግዳ የሆኑ ወሬዎች እና […]
↧
ሁለት ኢትዮጵውያን አትሌቶች ከአበረታች እጽ ጋር በተያያዘ ከሃገራዊና አለማቀፋዊ ውድድሮች ታገዱ
አትሌት ብርቱኳን አደባ እና አትሌት እዮብ አለሙ ለ4 ዓመታት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ እንዳይሳተፉ ታገዱ:: ዜናውን በቪዲዮ ለማየት እዚህ ይጫኑ የወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ሁለቱ አትሌቶች የተከለከለ መድኃኒት በመጠቀም የህግ ጥሰት በመፈፀማቸው ነው የኢትዮጵያ ብሄራዊ የፀረ አበረታች ቅመሞች ጽህፈት ቤት ውሳኔ የተቀጡት:: አትሌት ብርቱኳን አደባ በሪሁን በሻንጋይ ዓለም አቀፍ ማራቶን ውድድር ላይ “ኤግዞጂንየስ […]
↧
የተለቀቀው የአትሌት ጌጤ ዋሚ ቪዲዮ ብዙዎችን አሳዘነ
(ዘ-ሐበሻ) ጀግናዋ አልትሌት ጌጤ ዋሚ ለ18 ዓመታት ያህል በጓደኞቿ መተት እንደተደረገባት የሚያሳይና ቪዲዮ በማህበራዊ ድረገጾች ከተለቀቀ በኋላ ብዙዎችን አሳዘነ። አትሌቷ ለ18 ዓመታት የተደረገባት መተት ጤናዋን እና የምትወደው ትዳሯን እንድታጣ እንዳደረጋት፤ ታላላቅ ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ እግሮቿን እንደሚይዛት፤ ደብረብርሃን ላይ የሰራችው ሆቴል እንዲያስጠላትና የራሷ እንዳይመስላት፤ የ11 ዓመት ልጇ የ እርሳ እንዳትመስላት እንዳደረጋት ለመምህር ግርማ ስትናገር ቪዲዮው […]
↧