(ዘ-ሐበሻ) በሪዮ ኦሎምፒክ በ1500 ሜትር የሴቶች ውድድር ኢትዮጵያዊቷ ብርቅዬ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ሁለተኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የመጀምሪያውን የብር ሜዳሊያ አስገኘች::
ገንዘቤ ውድድሩን ወደ መጨረሻው አካባቢ ለመምራት ችላ የነበረች ቢሆንም በኬንያዋ አትሌት ፌዝ ኪፕዮጎን ተቀድማ ሁለተኛ ወጥታለች:: ኬንያዊቷ አትሌት ውድድሩን በ4:08.92 ስታሸንፍ ገንዘቤ 4:10.27 ለመግባት ችላለች:: አሜሪካዊቷ ጄኔፈር ሲምፕሰን በ4:10.53 በመግባት የነሐስ ሜዳሊያ አሸንፋለች::
ለሆላንድ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮያዊቷ ሲፋን ሃሰን ውድድሩን በአምስተኛነት ስታጠናቅቅ ኢትይዮጵያዊቷ ዳዊት ስዩም 8ኛ ወጥታለች::