Quantcast
Channel: ስፖርት | ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) - Latest Ethiopian News Provider
Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

ኢትዮጵያ ራሷ ባዘጋጀችው የሴካፋ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ በብሩንዲ ተሸነፈች

$
0
0

ethiopia

(ዘ-ሐበሻ) የመጀመሪያው ቀን ጨዋታዎች አሰተናጋጇ ኢትዮጵያ በሩዋንዳ ፤ዛንዚባር በቡሩንዲ 1ለ 0 በሆነ በተመሳሳይ ውጤት ተሸንፈዋል።

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ዛሬ የተጀመረው የ2015 ሴካፋ ዋንጫ (2015 CECAFA) ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በሜዳው እና በደጋፊው ፊት 1ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል::

ባለፈው ሳምንት በዲሞክራቲክ ኮንጎ በደርሶ መልስ ጨዋታ ተሸንፎ ከዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች የተሰናበተው ብሄራዊ ቡድናችን አሁን ያለበት ወቅታዊ አቋም በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል::

ብሔራዊ ቡድኑ ራሱ ባዘጋጀው ውድድር ላይ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት 1ለ0 መሸነፉ አሳሳቢ መሆኑን የሚናገሩት የስፖርት ተንታኞች በየፊናቸው መፍትሄ የሚሉትን ሃሳቦች በመሰንዘር ላይ ናቸው::

በኢትዮጵያ ዛሬ በተጀመረው የሴካፋ ዋንጫ በሩዋንዳ 1ለ0 ስትሸነፍ ዛንዚባርም እንዲሁ በብሩንዲ በተመሳሳይ 1ለ0 ተረታለች::

ኢትዮጵያና ሩዋንዳ ያደረጉት ጨዋታ ከረፍት በፊት 0ለ0 ተጠናቆ ሩዋንዳዎች በ54ኛው ደቂቃ ላይ ያገኟትን የቅጣት ምት ወደ ጎል ቀይረው አሸንፈው ወጥቷዋል::

የዛሬው ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታዲየም የተደረገ ሲሆን ውድድሩ በአዋሳና በባህርዳር ስታዲየሞች እንደሚቀጥሉ ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች አመልክተዋል::

በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን መሸነፍ የተናደደ አንድ ደጋፊ በዘ-ሐበሻ የፌስቡክ ገጽ ስሜቱን ሲገልጽ እንዲህ ብሏል

“ተከብረሽ የኖርሺው በሠውነት ቢሻው
ዮሃንስ መጣና አረገሽ እንዳሻው !”

The post ኢትዮጵያ ራሷ ባዘጋጀችው የሴካፋ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ በብሩንዲ ተሸነፈች appeared first on Zehabesha Amharic.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

Trending Articles