ሰለሞን ገ/መድህን የኢትዮጵያ የረጅም ርቀት ፈር ቀዳጅ የሆኑት አንጋፋው አትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ ዛሬ 100ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን አከበሩ። አትሌት ዋሚ ባደረጉት ውድድሮች 30 የወርቅ፣ 40 የብርና 10 የነሐስ ሜዳሊያዎችን አስገኝተዋል። አበበ ቢቂላ ወደ ሩጫ እንዲገባና በማራቶን ለኢትዮጵያ ሁለት ወርቅ እንዲያስገኝም የአትሌት ዋቢ ድጋፍ ከፍተኛ ነበር። የአበበ ቢቂላ አሰልጣኝ ሆነውም ሰርተዋል።
↧