የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከሶማሊያ ጋር ለ2017ቱ ከ20 በታች የአፍሪካ ዋንጫ ለመግባት ያደረገውን የመጀመረ የማጣሪያ ጨዋታ በ2ለ1 አሸነፈ::
ወጣት ብሔራዊ ቡድኑ ከጨዋታ ብልጫ ጋር ይህን ድል መቀዳጀቱን የስፖርት ተንታኞች ገልጸዋል::
የኢትዮጵያ ወጣት ብሔራዊ ቡድን የመልስ ጨዋታውን ከሶማሊያ ጋር ሲያደርግ ወደ መቋድሾ አያመራም:: እዚያ ባለው የጸጥታ ስጋት የተነሳ የመልስ ጨዋታው በገለለተኛ ሃገር የሚደረግ ይሆናል:: በዚህም መሰረት ቀጣዩ ጨዋታ ጅቡቲ ላይ ይደረጋል ሲሉ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታውቀዋል::
ብሄራዊ ቡድናችን በዛምቢያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሶማሊያ አቻውን አስተናግዶ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ሱማሊያ አንድ ጎል ከሜዳዋ ውጭ በማስቆጠሯ ጅቡቲ ላይ አንድ ለዜሮ ካሸነፈች ወደ ቀጣይ ዙር ልታልፍ ትችላለች:: ሆኖም ግን ብሔራዊ ቡድናችን ከሜዳው ውጭ የገባበትን የግብ ዕዳ ለመክፈል ጠንክሮ መጫወትና ጎል ማግባት ይጠበቅበታል::