Quantcast
Channel: ስፖርት | ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) - Latest Ethiopian News Provider
Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

አንቶኒ ማርሻል ለዛሬ (ማክሰኞ) የማን.ዩናይትድ እና ዌስትሃም ፍልሚያ የመሰለፍ ዕድሉ ምን ያህል ነው?

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ማን.ዩናይትድ ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ የሚወስደውን መንገድ የሚወስነው ዛሬ ማክሰኞ ከዌስትሃም ጋር ከሚያደርገው ጨዋታ ጋር ነው:: ከትናንት በስቲያ እሁድ አርሰናል ከማን.ሲቲ ጋር ነጥብ መጋራቱ ሲቲ በቻምፒዮንስ ሊግ ለመሳተፍ ያለውን እድል ማን.ዩናይትድ እንዲሸነፍ ከመጸለይ ጋር አያይዞበታል::
Manchester United v Sunderland - Premier League

በዘንድሮው ሲዝን ለማን.ዩናይትድ ወሳኝ ተጫዋች የነበረው አንቶኒ ማርሻል ነበር:: ይህ ወጣት ተጫዋች በእንግሊዙ ክለብ የመጀመሪያ ዓመት ተሳትፎው በስሙ 15 ጎሎችን አስመዝግቧል:: ይህ ተጫዋች ባለፈው ቅዳሜ ከኖርዊች ሲቲ ጋር በተደረገው የፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ለጨዋታው ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት በልምምድ ላይ ጉዳት ደርሶበት ሳይጫወት ቀርቷል:: ይህም ለማን.ዩናይትድ አጥቂ ክፍል ራስ ምታት ሆኗል::

የ እንግሊዙ ዝነኛ ታብሎይድ ዘሰን እንደዘገበው የውድድር ዓመቱ ምርጥ አጥቂ አንቶኒ ማርሻል ክለቡ ከዌስትሃም ጋር በሚያደርገው የሻምፒዮንስ ሊጉን ተሳትፎ በሚወስንበት ወሳኝ ጨዋታ ላይ አይደርስም:: በዚህም የተነሳ በአማካኝ ክፍል ሲጫወት የነበረው ሩኒ ወደ ፊት መጥቶ የማን.ዩናይትድን የፊት መስመር ይመራል ተብሎ ይጠበቃል::

አንቶኒ ማርሻልን በቀጣዩ እሁድ ከቦርንማውዝ ለሚደረገው የመጨረሻ የፕሪምየር ሊግ ጨዋታና ከዛ በመቀጠል ከክሪስታል ፓላስ ጋር ለሚደረገው የኤፍ ኤ ካፕ ፍጻሜ ፍልሚያ ለማድረስ የማንችስተር ዩናይትድ ሀኪሞች እየተረባረቡ እንደሚገኙ ዘሰን ዘግቧል:: ከዚህ በኋላ ሌሎች ተጫዋቾቻቸውን በጉዳት ማጣት የማይፈልጉት ቫንግሃል በተጫዋቾቼ ላይ በልምምድ ወቅት ጫና አላበዛባቸውም ብለዋል::


Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

Trending Articles