ስሜነህ ታደሰ | ለዘ-ሐበሻ ስፖርት
(ዘ-ሐበሻ) በፕሪምየር ሊጉ የመጨረሻው ጨዋታ ላይ ዛሬ ማንቸስተር ዩናይትድ ከበርንማውዝ ጋር ወሳኝ ጨዋታ የነበረው ቢሆንም በስታዲየሙ ውስጥ አሸባሪዎች ያስቀመጡት ሊሆን የሚችል አጠራጣሪ ቦርሳ በመገኘቱ ጨዋታው ለሕዝብ ደህንነት ሲባል መሰረዙ ተዘገበ::
ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት አነፍናፊ ውሾች በስታዲየሙ ውስጥ ይህ አጠራጣሪ ቦርሳን እንደጠቆሙ በሁለት ክንፍ በኩል ያሉ መቀመጫዎች በሙሉ ህዝብ እንዲወጣ ተደርጎ ነበር:: በምርመራውም ጨዋታው ዘግየት ብሎ ይጀምራል ተብሎ የታሰበ ቢሆንም ለሕዝብ ደህንነት ሲባል መሰረዙን የማን.ዩናይትድ ድረገጽ ዘግቧል::