Quantcast
Channel: ስፖርት | ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) - Latest Ethiopian News Provider
Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

አትሌት ኩለኒ ገልቻ በፍቅረኛዋ በስለት ተወግታ ተገደለች

$
0
0

Zehabesha-News.jpg
(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ስፖርት ክለብ በመካከለኛ ርቀት 800 ሜትር ተወዳዳሪ የነበረችውና በብሔራዊ ቡድን ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት ተመራጭ በመሆን የምትታወቀው የ19 አመትዋ አትሌት ኩለኒ ገለልቻ ከወንድ ጓደኛዋ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት በጓደኛዋ እጅ ህይወቷ አልፏል::

አትሌቷ ተስፋ ያላትና በጥሩ የአትሌቲክስ ውጤት ላይ የምትገኝ እንደነበረች የአለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኞች ማህበር ድረ ገፅ መረጃ ያሳያል ያለው የፌዴሬሽኑ ዘገባ በ800 ሜትር ሴቶች 2 ደቂቃ ከ06 ሰከንድ ከ68 ማይክሮ ሰከንድ የግል ምርጥ ሰዓት ነበራት ብሏል::

አትሌቷን የገደለው ወጣት ወዲያውኑ ለፖሊስ እጁን መስጠቱን ምንጮች ሲጠቅሱ አስከሬኗ በምኒሊክ ሆስፒታል ምርመራ ሲደረግለት ቆይቶ ግንቦት 5/2008 ዓ. ም. ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ላይ በትውልድ አካባቢዋ ኦሮሚያ ክልል አምቦ ከተማ የቀብር ስነስርአት እንደተካሄደ ተገልጿል::


Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

Trending Articles