Quantcast
Channel: ስፖርት | ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) - Latest Ethiopian News Provider
Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

በሪዮ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያን በማራቶን የሚወክሏት አትሌቶች ታወቁ

$
0
0

Mare dibaba ethiopia

 ስሜነህ ታደሰ | ለዘ-ሐበሻ ስፖርት

(ዘ-ሐበሻ) ሊጀመር 77 ቀናት የቀሩት አጓጊው የብራዚሉ ኦሎምፒክ ሃገራት የሚወክሏቸውን አትሌቶች በማሳወቅ ላይ ይገኛሉ:: ኢትዮያም ባለፈው ሳምንት በአጭር ርቀት ሩጫዎች የሚወክሏትን አትሌቶች አሳውቃ የነበረ ሲሆን የማራቶን ወኪሎቿን እስካሁን ስታሳውቅ ቀርታ ነበር::

ዘ-ሐበሻ ከዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ድረገጽ እንዳገኘችው መረጃ ከሆነ በሪዮ ኦሎምፒክ በማራቶን ኢትዮጵያን ከሚወክሉት ታላላቅ አትሌቶች መካከል የዓለም ሻምፒዮኗ ማሬ ዲባባ እንደምትገኝበት ታውቋል::

ማሬ ዲባባ ኦገስት 30, 2015 በቤጂንግ ቻይና በተደረገው 15ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ2:27:35 በመግባት አሸናፊ መሆኗ ይታወሳል::

ኦክቶበር 20, 1989 የተወለደችው ማሬ የማራቶን ቡድናችን መሪ ትሆናለች::
በወንዶች ተስፋዬ አበራ; ለሚ ብርሃኑ እና ፈይሳ ላሊሳ ሲመረጡ በተጠባባቂነት ቀነኒሳ በቀለ; አድሃነ የማነና ለሊሳ ዲሳሳ በማራቶን እንዲወክሉ ተመርጠዋል::

በሴቶች ማራቶን ማሬ ዲባባ; አበሩ ከበደና አሰለፈች መርጊያ ሲመረጡ በተጠባባቂነት ት ዕግስት ቱፋ እና ትርፌ ጸጋዬ ተመርጠዋል::

በሬዮው ኦሎምፒክ  206 ሃገራት ሲሳተፉ 42 ዓይነት ስፖርቶች ይካሄዳሉ::

ብራዚል ይህንታላቁን ኦሎምፒክ ለማዘጋጀት 37 የስፖርት ማከናወኛዎችን ገምብታለች::

መልካም ዕድል ለአትሌቶቻችን::


Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

Trending Articles