Quantcast
Channel: ስፖርት | ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) - Latest Ethiopian News Provider
Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

ሶማሊያዊው የአትሌት ገንዘቤ ዲባባ አሰልጣኝ ታሰረ

$
0
0

genzebe dibaba

(ዘ-ሐበሻ) የአትሌት ገንዘቤ ዲባባ አሰልጣኝ ጃማ ኤደን ስፖርተኞች ከሚወስዱት አበረታች ዕጽ ጋር በተያያዘ ተጠርጥሮ ስፔን ውስጥ መታሰሩ ተሰማ::

ገንዘቤ ከወራት ወዲህ በኢዩጂን፡ በኦስሎና ስቶክሆልም የሩጫ ውድድሮች የነበሯት ሲሆን ባልታወቀ ሁኔታ በነዚህ ውድድሮች ሳትሳተፍ መቅረቷ አይዘነጋም::

የዓመቱ ምርጥ አትሌትነትን እና ሌሎች ሽልማቶችን የጠቀለለችው ገንዘቤ የወቅቱ የ1 ሺህ 500 ሜትር የዓለም ሻምፒዮና ስትሆን ሶማሊያዊ ዜግነት ያለው አሰልጣኟ በስፔን በካታሎኒያ አትሌቶችን ሰብሰበው በሚያሰለጥኑበት አካባቢ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ መያዙን የፈረንሳዩ የዜና ወኪል ዘግቧል;:

ከሶማሊያዊው አሰልጣኝ ጋር እነማን አትሌቶች እንደተነካኩ የተዘገበ ነገር የለም::


Viewing all articles
Browse latest Browse all 419

Trending Articles