Quantcast
Channel: ስፖርት | ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) - Latest Ethiopian News Provider
Viewing all 419 articles
Browse latest View live

Sport: የፕሪሚየር ሊጉ ‹‹ክስተት›› ቡድን –ሌይስተር ሲቲ

$
0
0

city
ሼይላ ኬንት ባለፉት 40 ዓመታት የሌይስተር ሲቲን ትጥቅ በማፅዳት ሥራ ተጠምዳ ቆይታለች፡፡ በእነኚህ አራት አስርት ዓመታት ሌይስተር ሲቲ እንደ አሁኑ ስኬታማ ሆኖ ተመልክታ አታውቅም፡፡

የአሰልጣኝ ክላውድዮ ሪኒዬሪ ቡድን ከቅዳሜው ጨዋታ በፊት በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አናት ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ ይህንን የውድድር አመቱ መጀመሪያ ድረስ ማንም አስቦት አያውቅም ነበር፡፡

‹‹ባለፉት 40 ዓመታት ያመለጠኝ ሁለት ጨዋታዎች ብቻ ናቸው›› ይላል ጨዋታዎች ብቻ ናቸው ይላል ከ1971 ጀምሮ በሌይስተር ሲቲ በእግር ኳስ ተጨዋችነት እንዲሁም አሁን በአምባሳደርነት እየሰራ የሚገኘው አለንቢርቺናል፣ ‹‹እዚህ በነበረኝ ቆይታ 24 በሚደርሱ የቀብር ስነ ስርዓቶች ላይ ተሳታፊ ነበርኩኝ፡፡ የዓለማችን እድለኛ ሰው እንደሆንኩኝ መናገር አለብኝ፤ በክለቡ ቆይታዬ ምርጥ የምባል እግርኳስ ተጨዋች አልነበርኩም፡፡ በርካታ ጨዋታዎች አልተጫወትኩም፡፡

‹‹እዚህ በነበርኩበት ወቅት አስደሳች ጊዜያትን አሳልፌያለሁኝ፣ በአሁኑ ሰዓት ክለባችንን በአምባሳደርነት መምራቴ ያስደስተኛል ሆኖም ከተጫዋችነት ዘመኔ ይልቅ በአምበሳደርነት ያገለገልኩበት ዘመን የተባለ ነው፡፡
የእግርኳስ የስኬት አንዱ ምስጢር በጋራ አብሮ የመስራት ባህልን ማዳበር ነው የፅዳት ክፍሉ የዚህ አንድ አካል እንደሆነ ይታወቃል፡፡

‹‹ይህ ወቅት በሁሉም ዘንድ የሚወደድ ነው›› ችላለች የክለቡን ትጥቅ ፅዳት የምትቆጣጠረው ቬይላ፣ ‹‹ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ እናት ላይ የተቀመጥነው መቼ ነበር? በአሰልጣኝ ማርቲን ኦኔይል ዘመን በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዡ ወገብ ላይ ሆነን ፈፅመናል፣ ሆኖም ይህ አሁን የምንገኝበት ደረጃ የምንጊዜውም ምርጡ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ክላውዲዮ መጥቶ ሄሎ አለን፤ ከጣልያን ቼኮሌት ይዞልን መጣ፤ ጎክሃን (አንላር) ወደዚህ እንዲመጣ አደረገ፡፡ አጋጣሚው በጣም አስደሳች ነበር››

በሌይስተር ሲቲ አመጋገብ በጥንቃቄ እና ሳይንሳዊ ግብአቶችን ያሟላ ነው፤ ‹‹ለረጅም ዓመታት ውጣ ውረዱን ተመልክቻለሁኝ›› ይላል ለረጅም ጊዜ በምግብ ባለሙያነት ለክለቡ ያገለገለው ጋሪ ፔቶን፣ ‹‹አሁን በምንገኝበት ደረጃ ለመብቃት ብዙ ውጣ ውረዶችን አሳልፈናል›› ይላል፡፡ ለረጅም ጊዜ በምግብ ባለሙያነት ለክለቡ ያገለገሉት ጋሪ ፔቶን፣ ‹‹አሁን በምንገኝበት ደረጃ ለመብቃት ብዙ ውጣ ውረዶችን አሳልፈናል፣ የገንዘብ ችግር ተፅዕኖ አሳርፎብንም ነበር፡፡ ይህ ሁሉ አልፎ አሁን ያለውን ነገር ስመለከት የኩራት ስሜት ይሰማኛል››
በሜዳ ውስጥ የተጨዋቾች ታታሪነት በጣም ይገርማል፡፡ ተጨዋቾቹ በልምምድ ሜዳ ላይ ከመደበኛው ልምምድ ውጭ ተጨማሪ ሥራዎችን ይሰራሉ፡፡

‹‹በአሁኑ ሰዓት በክለቡ ውስጥ ያለው ስሜት ያስደስታል›› ይላል የቀኝ መስመር ተከላካዩ ዳኒ ሲምፕሰን፣ ‹‹ሁሉም ተጨዋቾች ከመደበኛው ልምምድ ውጭ ተጨማሪ ልምምድ እንሰራለን፤ እግርኳስ ከአእምሮ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ አሁን በጥሩ ስሜት ላይ እንገኛለን ነገር ግን አንድ ቦታ ላይ መቆም አንፈልግም››
ለሌይስተር ሲቲ ውጤታማ ጉዞ አንዱ ምስጢር ክላውዲዮ ራኒዮሪ እንደሆኑ ጥርጥር የለውም፣ ጣልያናዊው አሰልጣኝ ለእንግሊዝ እግርኳስ አዲስ አይደሉም፤ በቼልሲ አስደሳች ጊዜያትን አሳልፈዋል፤ በአገራቸው ጣልያን፣ ፈረንሳይ (ሞናኮ)፣ የግሪክ ብሔራዊ ቡድንን እና ስፔን አሰልጥነዋል፡፡

‹‹በእግር ኳስ ማሸነፍ፣ መሸነፍ እና አቻ ውጤቶች ቢኖሩም ተጨዋቾቼ በተመሳሳይ የአዕምሮ ጥንካሬ እንዲጫወቱ ስነግራቸው ቆይቻለሁኝ›› የሚል አስተያየትን የሚሰጡት ራኒዮሪ ‹‹በጭራሽ መዘናጋት አልፈልግም፣ ተጨዋቾቼ ከተዘናጉ ቡድኑ ሌይስተር ሲቲ እንዳልሆነ እነግራቸዋለሁኝ፣ እነርሱም ቢሆኑ ይህንኑ ጠንቅቀው ያውቃሉ›› በማለት ሁልጊዜም ቢሆን በተነቃቃ መንፈስ የሚጫወት ቡድን እንዲኖራቸው ያላቸውን ፍላጎት ጠቁመዋል››

በቼልሲ ሳሉ አፈራርቆ የማጫወት ፖሊሲን ይከተሉ የነበሩት ራኒዮሪ በሌይስተር ሲቲ አቀራረባቸው ተቀይሯል፤ (የማንቸስተር ዩናይትዱን ጨዋታ ሳይጨምር) ባለፉት 13 ጨዋታዎች ከቋሚ ተሰላፊዎች ዘጠን ያህሉ ዘጠኝ እና ከዚያ በላይ ጨዋታዎችን ፈፅመዋል፡፡

የቋንቋ ጉዳይ ሌላው ጥያቄ የሚነሳበት ነገር ነው፤ በቼልሲ ሳሉ በዚህ ረገድ ይቸገሩ የነበሩት ጣልያናዊ አሰልጣኝ አሁን በሌይስተር ሲቲ ስኬታማ ሆነዋል፡፡

‹‹በቼልሲ ሳለሁኝ ሁሉም ነገር የሚከናወነው በአስተርጓሚ ነበር፤ ያ ጊዜ ጋስ ፓዬት፣ ማርሴይ ዴሳይ እና ጂያን ፍራንኮ ዞላ በአስተርጓሚነት ያግዙኝ ነበር፤ አሁን ይህ እንደ አንድ ችግር አይነሳም ይላሉ የ64 ዓመቱ አሰልጣኝ፡፡

ባለፈው ዓመት ላለመውረድ ሲጫወት የነበረው ሌይስተር ሲቲ ዘንድሮ ፍፁም ተሻሽሏል፤ ራኒዬሪ እንኳን በዚህ ደረጃ የሚገኝ ክለብ በአደረጃጀቱ ተገርመዋል፡፡ ያም ቢሆን ግን በሌይስተር ሲቲ ስማቸው ልቆ የሚነሳውን ናይጅል ፔርሰን መርሳት አይገባም፡፡

‹‹በዙሪያዬ የሚገኙ ስታፎችን ስመለከት እገረማለሁኝ፣ የአካል ብቃት አሰልጣኞችን፣ የምልመላ አቅማችን፣ የቪዲዮ ትንታኔ… ሁሉም ነገር አስገራሚ ነው›› የሚል መረጃን የሚሰጡት በአሰልጣንነት የ30 ዓመት ልምድ ያላቸው ራኒዬራ ናቸው፤ ‹‹ሁሉም ነገር የተሟላ ከሆነ ለምን መቀየር ያስፈልገኛል፤ በአጠቃላይ ደስተኛ ነኝ››
ረዳት አሰልጣኙ ስቲቭ ዋልሽ ካለ ልዩ ተሰጥኦ ተጨዋቾችን ይመለምላል፤ ሪያድ ማህሬዝ አንዱ ነው፡፡ ለአማካይ ክፍሉ ጉልበት እና ኳስን በመንጠቁ ረገድ ምርጥ የሆነው ጓጎሎ ካንቴ ሌላው የሚጠቀስ ተጨዋች ነው፡፡

‹‹በዚህ አይነት መልኩ ምን ያህል ርቀት እንደምንጓዝ የማውቀው ነገር የለም፣ በአሁኑ ሰዓት የሚበርሩ ተጨዋቾች አሉን፤ ባለፉት 50 ዓመታት ከማውቀው ምርጥ የምልመላ ክፍል አለን፤ ነገሩ አስደሳች ነው›› ይላል አለን ቢርቼናል፡፡

The post Sport: የፕሪሚየር ሊጉ ‹‹ክስተት›› ቡድን – ሌይስተር ሲቲ appeared first on Zehabesha Amharic.


Sport: ቸልሲ ሞሪንሆን ለ2ኛ ጊዜ አባረረ

$
0
0

Jose Morniho

(ዘ-ሐበሻ) ቸልሲ አስልጣኝ ሆዜ ሞሪንሆን ለሁለተኛ ጊዜ አባረረ:: በፕሪምየር ሊጉ 16 ጨዋታ አድርገው 15 ነጥብ ብቻ የያዙት ሆዜ ሞሪንሆ ዛሬ የተባረሩት በቸልሲ የቦርድ ውሳኔ እንደሆነ ከወደ እንግሊዝ የተሰሙ መረጃዎች አመልክተዋል::

ፕሪምየር ሊጉን ካሸነፉ ከ7 ወር በኋላ የተባረሩት የፕሪምየር ሊጉ አድማቂ አሰልጣኝ ሆዜ ሞሪንሆን በተመለከተ ደይሊ ሜይል የተሰኘው ድረገጽ ባሰባሰበው የሕዝብ ድምጽ “ቸልሲ ሞሪንሆን ማባረር ነበረበት ወይ?” የሚል ጥያቄ አቅርቦ 57%ቱ ሕዝብ እድል ሊሰጠው ይገባ ነበር ማባረሩም መቆየር ነበረበት የሚል ምላሽ ሰጥተዋል::

ዘ-ሐበሻ ከ እንግሊዝ የዜና አውታሮች ባሰባሰበችው መረጃ መሠረት ሞሪንሆ ዛሬ ወደ ቸልሲ ልምምድ ስፍራ ኮብሃም ተጠርተው ከክለቡ ፕሬዚዳንት ብሩስ በክ እና ዳይሬክተሩ ዩጂን ተነቡአም ጋር ስብሰባ ያደረጉ ቢሆንም ለ10 ደቂቃ እንኳ ሳይነጋገሩ መሰናበታቸው ተነግሯቸዋል::

ሞሪንሆ ከዚህ ቀደም የቸልሲ አሰልጣኝ በነበሩበት ወቅት ተባረው ወደ ሪያል ማድሪድ አምርተው የነበረ ቢሆንም እንደገና በአብራሞቭች ተጠርተው ሥራቸው ከተመለሰላቸው በኋላ ዛሬ ለ2ኛ ጊዜ ተባረዋል::

ሞሪንሆ ሳይበሩ በፊት ዘ-ሐበሻ በስፖርት ገጿ የሚከተለውን ዘገባ አስነብባ ነበር… እዚህ ይጫኑ

The post Sport: ቸልሲ ሞሪንሆን ለ2ኛ ጊዜ አባረረ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ያከተመው የበላይነት |የእንግሊዝ ክለቦች በአህጉራዊ ውድድር ተዳክመዋል

$
0
0

 

champions

የእንግሊዝ ክለቦች ከ2004/05 የውድድር ዘመን ጀምሮ በአውሮፓ መድረክ የበላይነቱን ወስደው ቆይተዋል፡፡ ይህ የበላይነት እስከ 2011/12 የውድድር ዘመን ድረስ ዘልቋል፣ በዚህ የስምንት ዓት ጊዜ ውስጥ ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ሊቨርፑል እና ቼልሲ የውድድር ዘመኑ አሸናፊዎች ነበሩ፤ አርሰናል ደግሞ የፍፃሜ ተፋላሚ በመሆን የእንግሊዝ ክለቦች ኩራት ነበር፡፡ ከ2003/04 የውድድር ዘመን ጀምሮ እስከ 2011/12 የውድድር ዘመን ድረስ የእንግሊዝ ክለቦች በምድብ ማጣሪያ ሽንፈቱን ያስተናገዱበት ከፍተኛው ቁጥር አምስት ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ግን ከወዲሁ (ገና አንድ የምድብ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ እየቀረ) ሰባት ሽንፈቶች ተከስተዋል፡፡ (አራቱ ክለቦች በጋራ ያስመዘገቡት ሽንፈት መጠኑ እጅግ በጣም ከፍ ብሏል፡፡ ውጤቱ በዚህ ቁጥር ወደ ሶስት ዝቅ ሊል ይችላል፡፡ የእንግሊዝ ክለቦች አወራረድ ምን ይመስላል? ተከታዩ ፅሑፍ ምላሽ አለው፡፡

2000/05

የሊቨርፑል ተአምር የታየበት የኢስታንቡሉ የፍፃሜ ጨዋታ የመርሲሳይዱ ክለብ 3ለ0 ከመመራት ተነስቶ ቻ ከተለያየ በኋላ በመጨረሻም በመለያ ምት ያሸፈነበት ነበር፡፡ ‹‹የኢስታንቡሉ ተአምር›› የሚል ስያሜ ያገኘው የፍፃሜ ጨዋታ የእንግሊዝ ክለቦችን አነቃቅቷል፡፡ በግማሽ ፍፃሜው ቼልሲን ያሸነፈው የአሰልጣኝ የራፋ ቤኒቴዝ ቡድን ሻምፒዮን የሆነበት መንገድ ዛሬም ድረስ የመወያያ ርዕስ ሆኗል፤ በዚያ የውድድር ዘመን አርሰናል እና ማንቸስተር ዩናይትድን ያሸነፈው በውድድሩ በሁለተኛው ዙር ነበር፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡-4

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 2

2005/06

በስታድ ደ ፍራንስ አርሰናል በባርሴሎና 2ለ1 የተሸነፈበት የፍፃሜ ጨዋታ ፍፁም የሚያስቆጭ ነበር፡፡ የእንግሊዝ ክለቦችን ከሩብ ፍፃሜ ጀምሮ በመወከል ብቸኛ የነበረው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ታሪክ ሊሰራበት የተቃረበበት አጋጣሚ መቼም ቢሆን አይረሳም፡፡ ቼልሲ እና ሊቨርፑል ጉዟቸው ከሁለተኛው ዙር ሲገታ ማንቸስተር ዩናይትድ ከምድብ ማጣሪያው ማለፍ አልቻለም፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 03

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 1

2006/07

ሊቨርፑል በ2004/05 የውድድር ዘመን ለፍፃሜ ከቀረበው ኤሲ ሚላን ጋር በድጋሚ መገናኘቱ ትኩረትን ቢስብም የአቴንሱ የፍፃሜ ጨዋታ በጣልያኑ ክለብ 2ለ1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡ ሆኖም ሊቨርፑል፣ ቼልሲ እና ማንቸስተር ዩናይትድ ለግማሽ ፍፃሜ መድረሳቸው ለፕሪሚየር ሊጉ እንደ በጎ ዜና ሊወሰድ ይችላል፣ አርሰናል በሁለተኛው ዙር በፒ.ኤስ.ቪ አይንድሆቨን በደርሶ መልስ ተሸንፎ ከውድድሩ ውጭ ለመሆን ተገድዷል፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 4

2007/08

በሞስኮው ሉዝኒስኪ ስታዲየም ሁለት የእንግሊዝ ክለቦች ለፍፃሜ ቀርበው መደበኛው ሰዓት 1ለ1 ከተጠናቀቀ በኋላ ማንቸስተር ዩናይትድ ቼልሲን በመለያ ምት 6ለ5 አሸንፎ ከ1999 በኋላ የቻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ ኦነግ፣ በሩብ ፍፃሜው አርሰናልን ያሸነፈው ሊቨርፑል በግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ለቼልሲ እጅ ሰጥቶ ለፍፃሜ ለመግባት ሳይችል ቀርቷል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 4

2008/09

ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ቼልሲ፣ አርሰናል እና ሊቨርፑል በተሳተፉበት ውድድር ሊቨርፑል ከምድብ ማጣሪያው ሲወድቅ የተቀሩት ሶት ክለቦች ለግማሽ ፍፃሜ ደረሱ፣ ቼልሲ በባርሴሎና ተሸንፎ ለፍፃሜ ለመግባት የነበረው ህልም ሳይሳካ ቀረ፡፡ ማንቸስተር ዩናይትድ አርሰናልን አሸንፎ ለፍፃሜ ቢቀርብም በባርሴሎና ሮም ኦሎምፒክ ላይ 2ለ0 ተረታ፣ ሶስቱ የእንግሊዝ ክለቦች በምድብ ማጣሪያው በጋራ ሽንፈትን ያስተናገዱት በሁለት አጋጣሚዎች ብቻ ነበር፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 3

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች፡- 3

2009/10

ማንቸስተር ዩናይትድ፣ አርሰናል እና ቼልሲ ምድብ ማጣሪያዎችን ሲያልፉ ሊቨርፑል ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ተሳነው፡፡ በሁለተኛው ዙር ቼልሲ የውድድሩ አሸናፊ በሆነው ኢንተር ሚላን ሲሸነፍ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና አርሰናል ከሩብ ፍፃሜ ማለፍ ተሳናቸው፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 3

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች፡- 2

2010/11

ማንቸስተር ዩናይትድ ለፍፃሜ በቀረበበት የውድድር ዘመን በባርሴሎና ዌምብሌይ ላይ 3ለ1 ተሸንፎ ዋንጫ ለማንሳት የነበረው ህልም ሳይሳካ ቀረ፣ አርሰናል በሁለተኛው ዙር በውድድሩ አሸናፊ ባርሴሎና በተረታበት አጋጣሚ ቶተንሃም እና ቼልሲ ሩብ ፍፃሜ ድረስ መጓዝ ችለው ነበር፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 4

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች፡- 3

2011/12

በፕሪሚየር ሊጉ 6ኛ ደረጃን ይዞ የፈፀመው ቼልሲ በቻምፒዮንስ ሊጉ የፍፃሜ ጨዋታ ከባለሜዳውን ባየርን ሙኒክ በመደበኛው ጨዋታ 1ለ1 ተለያይቶ በመለያ ምት አሸንፎ ሻምፒዮን የሆነበት መንገድ በጣም አስገራሚ ነበር፡፡ ማንቸስተር  ዩናይትድ እና ማንቸስተር ሲቲ ከምድብ ማጣሪያው በተሰናበቱበት የውድድር ዘመን የአርሰናል ጉዞ በሩብ ፍፃሜው በመገታቱ ቼልሲ ረጅም ርቀት ተጉዞ ያስመዘገበው ስኬት የእንግሊዝ ኩራት እንዲሆን አስችሎታል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 2

ሩብ ፍፃሜውን የተቀላቀሉ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 1

2012/13

ቻምፒዮንስ ሊጉ በአዲስ መልክ ከ2003 ጀምሮ ከተዋቀረ በኋላ በሩብ ፍሜው አንድም የእንግሊዝ ክለብ ያልተገኘበት የውድድር ዘመን ነበር፣ ይህ የእንግሊዝ ክለቦች አቅም እየተዳከመ የመምጣት ምልክት አንድ አካል ተደርጎ ይወስዳል፡፡ አርሰናል እና ማንቸስተር ዩናይትድ ከሁለተኛው ዙር የተገታው ጉዟቸው ሩብ ፍፃሜ ለመግባት የነበራቸውን ህልም መና ሲያስቀረው ማንቸስተር ሲቲ እና ቼልሲ ከምድብ ማጣሪያው እንኳን ማለፍ አልቻሉም ነበር፡፡ ሲቲ በምድብ ማጣሪያው አንድም ጨዋታ አለማሸነፉ በብቃቱ ላይ ጥያቄ አስነስታሏል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 2

ሩብ ፍፃሜው የተቀባቀሉ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 0

2013/14

በሊዝበን ስታድ ደ ሉዝ ሁለቱ የማድሪድ ክለቦች ለፍፃሜ ቀርበው ሪያል ማድሪድ ለ10ኛ ጊዜ ይህንን ዋንጫ ማንሳት ችሏል፣ ባርሴሎና ደግሞ የሩብ ፍፃሜ ተፋላሚ ሆኖ በአትሌቲኮ ማድሪድ ያስተናገደው ሽንፈት ግማሽ ፍፃሜ እንዳይገባ አድርጎታል፡፡

ማንቸስተር ዩናይትድ ማንቸስተር ሲቲ፣ አርሰናል እና ቼልሲ ረጅም ርቀት ለመጓዝ የነበራቸው እቅድ የምዕራ ለንደኑን ክለብ ብቻ ግማሽ ፍፃሜ አድርሶ የቀሪዎቹን ሶስት ክለቦች ጉዞ ከሁለተኛው ዙር በላይ እንዳይጓዝ አድርጓል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 4

ሩብ ፍፃሜውን የተቀላቀሉ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 1

2014/15

በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ አንድም የእንግሊዝ ክለብ በሩብ ፍፃሜ ያልተስተዋለበት የውድድር ዘመን ነበር፡፡ አርሰናል፣ ቼልሲ እና ማንቸስተር ሲቲ ወደ ሁለተኛው ዙር ሲገቡ ሊቨርፑል ከምድብ ማጣሪያው እንኳን ማለፍ አልቻለም፡፡ በአንፃሩ ከስፔን ክለቦች ሶስቱ ሩብ ፍፃሜ ደርሰዋል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 3

ሩብ ፍፃሜ የገቡ የሊጉ ክለቦች፡- 0

The post Sport: ያከተመው የበላይነት | የእንግሊዝ ክለቦች በአህጉራዊ ውድድር ተዳክመዋል appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ኢንተርናሽናል የእግር ኳስ ዳኛው ለሚ ንጉሴ ለአንድ አመት ታገዱ

$
0
0

lemi  Niguse

ኢትዮ-ኪክ እንደዘገበው ኢንተርናሽናል አልቢትር ለሚ ንጉሴ ትላንት ኢትዮጵያ ቡና ከደደቢት ባደረጉት የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታ በፈፀሙት የዳኝነት ስህተት ለ1 አመት ከስራቸው ታግደዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ ቡና ያገኝውን የፍፁም ቅጣት ምት በቅርበት አስተውለው ጨዋታውን እንዲቀጠል ማድረጋቸውን ተከትሎ ደደቢቶች በፈጣን የመልሶ ማጥቃት ኳሷን ኢትዮጵያ ቡና መረብ ላይ አሳርፈዋል። ኢንተርናሽናል አልቢተር ለማ 2015 በCAF የክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ የመጀመሪያ ዙር የሱዳኑን አል ማላኪያ እና የናጄሪያውን ካኖ ፒሊራ ጨዋታ መርተዋል፤ ከዚህ በተጨማሪም በ2015 የCAF ከ20 አመት በታች ግብፅ እና ኮንጎ ያደረጉትን ጨዋታ በ4ኛ ዳኛንነት ተሳትፈዋል።

The post Sport: ኢንተርናሽናል የእግር ኳስ ዳኛው ለሚ ንጉሴ ለአንድ አመት ታገዱ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: የአልጄሪያው ኤምሲ አልጀር ክለብ በኢትዮጵያዊው አጥቂ ሳልሀዲን ሰኢድ ላይ ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት ሊጥልበት ነው

$
0
0

salahdin
ኢትዮኪክ ኦፍ እንደዘገበው:-

* ሳላ ኢትዮጵያ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ ሳልሀዲን ሰኢድ ከአልጄሪያው ኤምሲ አልጀር ጋር ለሁለት አመት ለመጫወት የነበረው ውል ለአምስት ወራት ብቻ ዘልቆ ከክለቡ ጋር ባለፈው ሳምንት መለያየቱ ይታወሳል።

በግብፁ አል አህሊ ረጅም ወራቶችን በጉዳት ካሳለፈ በኃላ የአልጄሪያውን MC-አልጀር የተቀላቀለው ሳልሀዲን በ5 ጨዋታዎች በአጠቃላይ 200 ደቂቃዎችን ተቀይሮ በሜዳ ውስጥ ቢቆይም ጎል እና መረብ ሳይሳኩለት ቀርተዋል።

ከአልጀሪያ የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚያሳዩት የአልጄሪያው ኤም ሲ አልጀር ክለብ ከ USMA ጋር ባደረጉት የአልጀረስ ደርቢ ጨዋታ ላይ ሳልሀዲን ሰኢድ ከስፖርታዊ ጨዋነት ውጪ የሆኑ ድርጊቶችን አሳይቷል በሚል ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት ለማስተላለፍ የክለቡ የዲስፒሊን ኮሚቴው በቀጣዪ ሳምንት ስብሰባ ጠርቷል።

እንደ መረጃው ከሆነ በእለቱ በተደረገው የደርቢ ጨዋታ ላይ ሳልሀዲን ከጉዳቱ አገግሞ ጥሩ አቋም ላይ መገኘቱን ለተቃራኒው ክለብ USMA ለማሳየት መፈለጉን እና ከዚህ ከደርቢ ጨዋታው በፊት ሳልሀዲን ከUSMA ክለብ ጋር ስሙ ተንስቷል የሚለው መረጃ በስፋት በመወራቱ በደርቢ ጨዋታው ላይ በምክትል አሰልጣኙ ትህዛዝ ሳልሀዲንን አሟሙቆ ሊገባ ሲል ዋናው አሰልጣኙ አሳባቸውን ቀይረው ወደ ወንበሩ እንዲመለስ ያስተላለፉትን ትህዛዝ ሳልሀዲንን ክፉኛ ተበሳጭቶ በወቅቱ ላሳያው ያልተገባ ፀባይ የገንዘቡ ቅጣት እንደሚጠብቀው ዘገባው የሚያመለክተው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ ሳልሀዲን ሰኢድ በአሁኑ ሰአት ከቤተሰቦቹ ጋር በአገሩ ምድር ኢትዮጵያ ይገኛል።

The post Sport: የአልጄሪያው ኤምሲ አልጀር ክለብ በኢትዮጵያዊው አጥቂ ሳልሀዲን ሰኢድ ላይ ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት ሊጥልበት ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ትውልደ ኢትዮጵያዊው ታዳጊ ወጣት ለባርሴሎና ክለብ ፈረመ

$
0
0

anwar madera

[በተሻገር ጣሰው]

አንዋር ማዴራ ይባላል በፈርነጆቹ አቆጣጠር ማርች 2003 ላይ ነበር በመዲናችን አዲስ አበባ የተወለደው ::
ገና ታዳጊ ህፃን እያለ በማደጎ ወደ ስፔን ተጎዘ በስፔን ቆይታውም ገና ከህፃንነቱ ጀምሮ ለእግር ኳስ ልዩ ፍቅር በመኖሩ ከኢትዮጵያ ወስደው የሚያሳድጉት ቤተሰቦቹ ፍላጎቱን ለማሞላት ወደ እግር ኳስ አካዳሚ አስገቡት ::ልክ አስራ አንድ አመቱ ሲሆነው ከአስራ ስድስት አመት በታች ሴልታ ቪጎን ክለብ ተቀላቅሎ መጫወት ጀመረ::

አንዋር አሁን አስራ ሶስት አመቱ ነው:: ከወደ ስፔን የተሰማው ዜና እንደሚያስረዳው በትውልድ ኢትዮጵያዊው የሆነው አንዋር ማዴራ የባርሴሎና ክለብ የበላይ ጠባቂዎችን በአጨዋወት ጥበብ በመማረኩ የተነሳ ሴልታ ቪጎን ክለብ ለቆ ከ16 አመት በታች ለባርሴሎና ክለብ እንዲጫወት ማስፈረማቸውን ነው የተዘገበው::

ተጫዋቹ በያዝነው በፈረንጆቹ አዲስ አመት ጨዋታውን እንደሚጀምርና ከ3 አመት በሆላ ለዋናው ባርሴሎና ክለብ መጫወት እንደሚፈልግ ምኞቱን ተናግሯል::

ለትውልደ ኢትዮጵያዊው አንዋር ማዴራ ያሰበው እንዲሳካለት መልካም ምኞታችን ነው

The post Sport: ትውልደ ኢትዮጵያዊው ታዳጊ ወጣት ለባርሴሎና ክለብ ፈረመ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአርሰናል ተጫዋቾች በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ መልካም ገና ይሏችኋል | Video

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) “የኃይሌ ገብረሥላሴ የብሔራዊ ቡድኑን የማሰልጠን ጥያቄ ድጋፍ ያሻዋል”

$
0
0

የምን ጊዜም ምርጡ አትሌታችን ሀይሌ ገብረስላሴ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ቡድንን ለማሰልጠን በሚዲያ አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ የሀይሌም ፍላጎትና ሀሳብ በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ ሀይሌ በኢትዮጵያ ሳይሆን በአለም ዝነኛ ስፖርተኛ ነው፡፡ 27 ሪከርዶችን የሰባበረ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ የአስር ሺ ሜትሩን ድል መልሶ ያመጣና በሁለት ተከታታይ ኦሎምፒክ ባለድል ያደረገን ብርቅዬ አትሌታችን ነው፡፡ ሀይሌ ‹‹ይቻላል›› በሚለው የማነሳሻ ሀሳቡም ይታወቃል፡፡ ማንኛውም ነገር ጠንክሮ ከተሰራ ‹‹ይቻላል›› የሚል አቋም አለው፡፡ እሱም ይሄን መንገድ ለሌሎች በማሳየት አርአያ በመሆን ይታወቃል፡፡ ሀይሌ ሰሞኑን ለዚህ ሀሳብ ምን አነሳሳው ሲባል በኢትዮጵያ ወስጥ እግር ኳስ ተወዳጅ ነው፡፡

Ethiopia's long distance runner and marathon world record holder Haile Gebrselassie

ህዝቡ ለእግር ኳሱ ምን አይነት ፍቅር እንዳለው ያውቃል፡፡ ነገር ግን በእግር ኳሱ ደካማ ውጤት የህዝቡን ብሶትና ሮሮ(እሱም ከህዝቡ አንዱ አዛኝ ነው) በመመልከት የበኩሉን ሀገራዊ አስተዋጽኦ ለማድረግ እንደሆነ ይታመናል፡፡ እሱ በውድድር አለም በቆየበት ተሸናፊ ሳይሆን አሸናፊ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ህዝብ ከዳር እስከ ዳር አስደስቷል፤አስጨፍሯል፡፡ ሀይሌ አሳፍሮን አያውቅም፡፡ ለህዘቡ ቃል የገባውን ያደርጋል፡፡ በአትሌቲክስ አለም አደባባይ የኢትዮጵያ ባንድራ ሲውለበለብ በእግር ኳሱ ግን ይሄ ነገር የለም፡፡ ሀይሌም በአትሌቲክሱ ህዝቡ እንደረካና እንዳተደሰተ ‹‹ይቻላል ›› በሚለው መርሁ በእግር ኳሱ ይሄ ነገር እንዲኖር ይፈልጋል፡፡ እግር ኳስ ብሄራዊ ድኑ ከ60 እና 70 ደቂቃ ጀምሮ እንደሚዳከምና የአካል ብቃት ችግር እንዳለባቸው ገልጾ ይሄ ነገር እንዲቀረፍ እሱ የአካል ብቃት አሰልጣኝ ሆኖ ቢመደብ ለውጥ እንደሚመጣ ተናግሯል፡፡ እሱ ፈቃደኝነቱን አሳይቷል፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምላሽ ይጠበቃል፡፡

 

ሀይሌ ብሄራዊ ቡድኑ እንዲሰጠው ድጋፋችን መስጠት ይኖርብናል፡፡ ሀይሌ ብሄራዊ ቡድን ለማሰልጠን የጠየቀው እንደሌሎች አሰልጣኝ ደሞዝ እየተከፈለው ለማገልገል አይደለም፡፡ በብሄራዊ ስሜት ተነሳስቶ ብሄራዊ በድኑ ውጤታማ ሆኖ ህዝቡ እንዲደሰት ለማድረግ ነው፡፡ እሱ ደግሞ በኢንዱራንስ ስራ የታወቀ ነው፡፡ከዚህ በፊት ክሩገር የተባለ የጊዮርጊስ አሰልጣኝ ክለቡ በዛማሌክ ነጥብ ጥሎ ከወድድር ሲወጣ ‹‹የኢትዮጰያ ተጫዋቾች ከ60 ደቂቃ በላይ መጫወት አይችሉም›› ብሎ ተናግሯ ፡

፡የሀይሌም ሀሳብ ተመሳሳይ ስለሆነ ሀይሌ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ እድሉ ሊሰጠው ይገባል፡፡ሀይሌ ከምንም ተነስቶ እንዲህ እንዳላለ ይታወቃል፡፡ ብዙ ነገር ከመረመረ በኋላ ጥያቄውን እንዳቀረበ ነው፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ዙሪያ ጥናት አድርገው አማራጭ ሀሳብ አለን ለሚሉ ፌዴሬሽኑ እድሉን ሊሰጥ ይገባል፡፡ ሀይሌም ከዚህ ጥያቄ አቅራቢዎች አንዱ ነው፡፡ነገር ግን ሀይሌ ችግሩ የአካል ብቃት ነው ብሏል፡፡እሱ አሰርቶ ለውጥ ከሌለ ችግሩ ‹‹እኔ ያልኩት አልነበረም›› ብሎ ለህዝቡ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡ አሱ የሚለውን አሰርቶ ውጤት ከሌለ ሌላ ነገር ውስጥ መግባት የለበትም(አስተዳደር፤አደረጃጀት፤ከታች ወርደን እንስራ የመሳሰሉት እንዳይደረደሩ) ፌዴሬሽኑ አማራጭ ሀሳብ ያላቸውን አቀርቦ ማሰራት አለበት፡፡ የሀይሌንም ሆነ የሌላውን ጥያቄ ‹‹ብሄራዊ ቡድኑ መሞከሪያ አይደለም›› ብሎ በር መዝጋት የለበትም፡፡ ምክኒያቱም አሁን እየተሰጠ ያለው ስልጠና በራሱ እየተሞከረ ነው ያውም 60 አመት ፡፡ ይህ ስልጠና 60 አመት ተሞክሮ ምንም ነገር አላስገኘም፡፡ ስለዚህ አማራጭ ሀሳብ ሲመጣ መሞከሪያ አይደለም በሚል ፌዴሬሽኑ ሌሎችን ሀሳብ መቃወም የለበትም፡፡(በእርግጥ የሀይሌ አማራጭ አይደለም) እናም ለሀይሌ ድጋፍ ስጡ፡፡ ግን ሀይሌም ችግሩ አካል ብቃት ብቻ ነው ብሎ ከመግባቱ በፊት ነገሮችን መዝኖና አመዛዝኖ መግባት አለበት፡፡

አካል ብቃት ለእግር ኳስ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡አንድ ተጨዋች ለጓደኛው አቀብሎ ያንን ለመቀበል መሮጥ አለበት፡፡90 ደቂቃ ለመጫወት ለእግር ኳስ አስፈላጊ ተብሎ የታመነበትን መስራት አለበት፡፡ ነገር ግን ለእግር ኳስ የሚስፈልገውን ነገር ሰርተን ብልጫ ከተወሰደብን ሌሎች ነገሮችን ከሌላ አቅጣጫ መመርመር አለብን፡፡ሀይሌ እንደሚያውቀው በረጅም ርቀት ሩጫ ውጤታማ ነን፡፡ ነገር ግን 100 እና 200 ሜትር በአፍሪካ ማሸነፍ ብቻ ሳይሆን ሚኒማ ማምጣት እንዴት እንደቸገረን ያውቃል፡፡ ሀይሌ በተወዳዳሪነት ጊዜው የጋና እና የናጀርያ ሯጮችን ከእሱ ጋር ሲወዳደሩ አይቷል እንዴ? አላየም፡፡ የናጀርያና ጋና አትሌቶች በኦሎምፒክ በሺ0 እና 5 ሸ ውጤት ሊያመጡ ቀርቶ ሚኒማ እንኳን የላቸውም፡፡ እነርሱ ሳይስሩ ቀርተው ነው እንዴ? የሚያሰራቸው ሰው አጥተው አይደለም፡፡ ጎበዝ አሰልጣኝ አላቸው፡፡ ሀይሌም እንደሚያውቀው ብዙ ጊዜ የናይጀርያና ጋና አትሌቲክስ ኢንስትራክተሮች ናቸው እኛን አትሌቶት አሰልጣኞች የሚያሰለጥኑት ፡፡ ይህን ያህል ብቃት ያላቸው አሰልጣኝ እያላቸው በረጅም ርቀት ሩጫ ሰው ማፍራት አልቻሉም ፡፡ ነገር ግን ናይጀርና ጋና በአጭር ርቀት ሩጫ ኦሎምፒክ ፋይናሊስት እስከመሆን የደረሱ ናቸው፡፡ በፍሪካ በሴትም በወንድም በ100 እና 200 ሻምፒዮና ናቸው፡፡ እንግዲህ እነርሱ በአጭር ርቀት ተፈጥሮን ጥገኛ ባደረገ መልኩ ሰርተው ውጤት አመጡ ፡፡በረጅም ርቀት ሞከሩ አልቻሉም ፡፡እኛም በረጅም ርቀት ተፈጥሮን ጥገኛ ባደረገ መልኩ ሰርተን ውጤት አመጣን፡፡ በ100 እና 200 አስቸጋሪ ሆነብን፡፡

እንግዲህ እግር ኳስ ፍጥነትና ጉልበት ስለሚጠይቅ ይሄን ነገር እናሟላለን ወይ ብለን ስንጠይቅ እንደማናሟላ በአትሌቲክሱ እያየን ነው፡፡ስለዚህ እነ ናጀርያና ጋና ጋር ስንገጥም የሚበልጡን በዚህ ከሆነ ከዚህ ነገር መውጣት እንጂ ሁል ጊዜ እዛ ውስጥ መንቦራጨቅ የለብንም፡፡ ፍጥነት ጉልበት ለእግር ኳሱ አስፈላጊ ነው፡፡ ለፍጥነት ማሻሻያ ተብሎ በእግር ኳሱ ውስጥ በስልጠናው የተቀመጡ ነገሮች አሉ(አካል ብቃት ውስጥ ስለሚመደብ) ለዚህ የሚሆን ልምድ ሰርተን መብለጥ ካልቻለን ይሄን በሌላ መተካት ነው፡፡ምክኒያቱም ለእግር ኳስ አስፈላጊ ነው ተብሎ በሚታመንበት ነገር ብልጫ ከተወሰደብህ ይሄን በሌላ መተካት ነው፡፡እኛም ማድረግ ያለብን ፍጥነትን በሌላ መተካት ጉልበትን በሌላ መተካት እንጅ እዛ ውስጥ ሆነን እኝኝኝኝኝኝኝኝ ……ብንል ምንም አናመጣም፡፡ብዙ የውጭ አሰልጣኞች መጥተው ቴክኒክ አላችሁ የአካል ብቃት ነው ችግራችሁ ይሉና ያንን ደካማ ነገር ለመሸፈን የአካል ብቃት ያሰሩና ችግሩ አይቀረፍ፡፡ሀይሌም እንደነዛ ሰዎች የአካል ብቃት ችግር መሆኑን አይቷል እሱም እንደሌሎቹ እዛ ውስጥ ያለውን መፍታት ሳይሆን ማባባስ ይሆናል፡፡እስካሁን የተበላሸነው እነ ናይጀርያ ጥሩ በሆኑበት እነርሱን መግጠማችን ነው ችግር ያመጣብን፡፡ እኛ ጥሩ በሆንበት ነገር አሰልጥኞ የተሻለ እንድንሆን የሚያድርግ ሰው ነው የሚያስፈልገው፡፡39 የውጭ አሰልጣኝ አምጥተን በዚህ መንገድ ሰርተን አልተለወጥንም፡፡ በተለይ ከምእራብና ሰሜን አፍሪካ ጋር ስንጫወት ይህ ነገር ጎልቶ ይወጣል፡፡ እነርሱ በተፈጥሮ ከእኛ የተሻለ ጉልበት አላቸው፡፡ብቻ ለብቻ ስንገኛኝ እነርሱ በዚህ የተሸለ ስለሆኑ ይበልጡና ፡፡ በጉልበት ሲያሹን ሲሸራርፉን እየተዳከምን እንሄዳል፡፡ያን ጊዜ ኢንዱራንሳችንም ይጠፋል ፡፡ ሀይሌ በራሱ በኩል በሩጫ ያለውን አካል ብቃት ነው ያየው፡፡ ሩጫ ዝም ብሎ መሮጥ ነው ንክኪ የለውም ፡፡ እየተገፈታተሩ እየተደባደቡ ቢሮጡ ለነሀይሌም ያስቸግራል፡፡

ባለፈው ከ9 ወር በፊት በአ/አ ስታዲየም ፌስቲቫል ጨዋታ እነ ቀነኒሳን ጨምሮ አትሌቶች እግር ኳስ ሲጫወቱ ምን ያህል እንደተቸገሩ ታይቷል፡፡ በ1992 ዓ.ም ለሲድኒ ኦሎምፒክ የሚዘጋጀው ቡድን በስታዲየም ልምምዱን በመሮጫ በትራኩ ላይ ያደርጋል፡፡ የእግር ኳስ ብሄራዊ በድኑ እነ ኩኩሻ፤ ሚኬሌ ሌሎችም ሜዳው ላይ እየተለማመዱ ነው፡፡ ትራኩን ዳኞች ኩፐር ቴስት ስለሚፈተኑበት ለ12 ደቂቃ ያህል አትሌቶቹ ፈቃድ ተጠይቀው ለቀቁላቸው ፡፡ አትሌቶቹ ሜዳ ውስጥ ገብተው ከብሄራዊ እግር ኳስ ቢድን ጋር ጫወት ጀምሩ፡፡ ‹‹ትችሉናላችሁ አትችሉንም›› በሚል ተፎካከሩና ተጋጠሙ፡፡ቀድመው የደከሙት እነ ሀይሌ የነበሩበት አትሌቶች ናቸው ፡፡ አትሌቶቹ ታክል ሲገቡ፤ ሲገፈታተሩ፤ በአጭር ቦታ ሲመላለሱ፤ ኳሱን ሲገፉ፤ ለመንጠቅ ሲታገሉ ተዳከሙ ፡፡ የእግር ኳስ ተጫዋቾቹ ግን አልደከማቸውም፡፡ አትሌቲክስ ውስጥ ይሄ ነገር የለም፡፡ እግርኳስ ውስጥ አብዛኛው ነገር ንክኪው ነው፡፡ ንክኪው ጉልበት ስለሚጠይቅ ይሄ ነገር ያዳክመናል ያን ጊዜ ቡድናችን ሲዝረከረክ ተዳከሙ ይባላል፡፡ መዳከሙ አይቀሬ ነው ፡፡ ንክኪው ጉልበት ይጠይቃል ይበዘብዛል ፡፡ንክኪው የሚመጣው ብቻ ለብቻ ባለው ግንኙነት ነው፡፡መጀመሪያ ብቻ ለብቻ የምንገናኝበትን ነገር ካስቀረን ስለ ሌላው ነገር መቅረፉ አስቸጋሪ አይሆንም፡፡የብቻ ለብቻውን ነገር በረዳት ማስቀረት ይቻላል፡፡እኛ ቴክኒኩ አለን፡፡ ቴክኒኩ ደግሞ ረዳትን ለመጠቀሚያ ዋነኛው መሳሪያ ነው፡፡

ስራዎቻችን እዚህ ላይ አተኩረን ይሄንን ለማገዝ የሚያሰችል አካል ብቃት ከተሰጠ ችግሩ ይፈታል፡፡ነገር ግን አሁን ሀይሌ እንደሚለውና ሌሎችም የውጭ አሰልጣኞች እንዳሰሩት ጥሬ አካል ብቃት ስራ ለምእራብና ሰሜን አፍሪካ ቡድኖች አሳልፎ የሚሰጠን ነው፡፡ለሜክሲኮ ኦሎምፒክ ማጣሪያ የእግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ተጋባዥ ሆኖ ሄደ፡፡ እግር ኳስ ቡድኑም አትሌቲክሱም ወንጂ ላይ ይለማመዱ ነበር፡፡ አበበ ቢቂላ እግር ኳስ ስለሚወድና አልፎ አልፎ ለክፍሉ ስለሚጫወት እየገባ ይጋጠም ነበር ነገር ግን እየደከመው ይወጣ ነበር፡፡ አበበ ሀይልና ትንፋሽ በሚጠይቀው ሩጫ ነው የሚታወቀው፡፡ ነገር ግን በእግር ኳሱ ውስጥ ባለው አካል ብቃት አልቻለበትም፡፡ኤፍሬም ሀይሌ ለጊዮርጊስ፤ ሙገር፤ እርሻና ለወጣት ቡድን ተጫውቷል፡፡ አፍሬም 14 አመት እግር ኳስ ተጫውቶ ካቆመ በኋላ አሁን በማራቶን እየሮጠ ነው፡፡የተሻለ ሰዓትም አለው፡፡ኤፍሬም በእግር ኳስ እንደማንኛወም ተጫዋች ይዳከማል፡፡ ነገር ግን በአትሌቲክሱ ውጤታማ ነው(የእግር ኳስ ተጨዋቾቻችን የኢንዱራንሱ ችግር እንደሌለባቸው የኤፍሬም ተሞክሮ ይነግረናል)፡፡ ሀይሌም እነዚህን ነገሮች መርምሮ መግባት እንዳለበት ነው፡፡፡ሀይሌ በእግር ኳስ አሰልጥኖ አያውቅም ግን ጎበዝ አትሌት ነው ፡፡ሀይሌን ውጤታማ ያደረጉት ዶክተር ወልደመስቀል ናቸው፡፡ከሀይሌ ይልቅ በማስልጠኑ ዶክተር ይሻላሉ፡፡ ድሮ አቶ ይድነቃቸው ብዙ ጊዜ ቡድኑ በምእራብ ቡድኖች ሲሸነፍና በአካከል ብቃት ተዳክሞ ሲታይ እነንጉሴ ሮባ ለብሄራዊ ቡድኑ የአካል ብቃት አሰልጣኝ እስከመሆን ደርሰው ነበር፡፡ያኔ ንጉሴ በአትሌቲክሱ ውጤታማ ነበሩ፡፡፡፡ዶከተር ወልደመስቀል ለሰባተኛ አፍሪካ ዋንጫ የተጫወተውን ቡድን ያዘጋጁት እሳቸው ነበሩ፡፡

ቡድኑ በሶስቱ ጨዋታ ተዳክሞና ተበልጦ ነው የታየው ፡፡በአይቮሪኮስት 6ለ1 ተሸነፈ (ይሄ እስካሁን በአፍሪካ ሪከርድ ነው) በምድብ ጨዋታ 12 ግብ ተቆጠረብን(ይሄም እስካሁን ሪከርድ ነው፡፡በምድብ ጨዋታ 12 ግብ በአፍሪካ ዋንጫ 12 የተቆጠረበት የለም) ቡድኑ ሜዳ ላይ የምእራብ አፍሪካ በድኖችን መቋቋም አልቻለም፡፡ዶከተር ወልደመስቀል ከአካል ብቃቱ አሰልጣኝነት ሌላ ጊዮርጊስን ዋናው ቡድን አሰልጥነዋል ፡፡(እነመንግስቱ ወርቁ የነበሩበትን)ካምፓላ ሲቲ በተባለ የኡጋንዳ ክለብ 4ለ0 ሲሸነፍ አሰልጣኝ ነበሩ፡፡ከዚያ በኋላ ሙሉ ለሙሉ ወደ አትሌቲክሱ ገቡ ፡፡ግን እሳቸውም ሆነ ንጉሴ የተናገሩት (ተጨዋቹ ለእግር ኳሱ ክፍያ አያገኙም፤በሳምንት ሁለት ጊዜ ብቻ እየተሰራ ለውጥ አይመጣም፤በካምፕ መቀመጥ አለባቸው፤መደበኛ ስራ መስራት የለባቸውም ያን ጊዜ ከስራ እየመጡ ትሪኒንግ ይሰሩ ነበር) ያን ጊዜ ይሄ ነገር ቀረበ፡፡ አሁን እነዚያ ችግሮች ሁሉ ተፈትተዋል ሜዳ ላይ ያለው ድክመቱ ግን እንደ ትላንትናው ነው፡፡ ዶክተር በእግር ኳሱ ብዙ ከሰሩ በኋላ ለውጥ ስላልተገኘ ወደ አትሌቲክሱ መጡ ፡፡ እዚያ ውጤታማ ሆኑ፡፡ ከአትሌቲክሱ አሰልጣኝ ሌላ እነ እስጢፋኖስን የመሰሉ የቦክስ አሰልጣኞች ለብሄራዊ ቡድኑ የአካል ብቃት ሆነው ሰርተዋል ግን በዚህ በኩል ያለው ችግር አልተቀረፍም ፡፡

ሀይሌም ከነ ንጉሴ ሮባ ከነወልደመስቀልና ከሌሎችም(በእግር ኳሱ ሰሩ) የአትሌቲክስ አሰልጣኞች በኋላ እነደነርሱ ችግሩ አካል ብቃት ነው ብሎ መጥቷል፡፡ለማኛውም ተሰጥቶ ሞክሮ ትክክለከኛውን ነገር ሊነግረን ይችል ይሆናል፡፡ወደ ስራው ከመግባቱ በፊት የነዶክተር ወልደመሰቀልን ተሞክሮ አይቶ እሳቸውን ጠይቆ ቢጋባ የተሻለ ነው፡፡ በእግር ኳሱ ያለው ችግር ግን ሀይሌ ከሚለው መውጣት እንጅ ሀይሌ ችግር ነው ባለው በኩል መስራት እንዳልሆነ የትላንቱ ተሞክሮ ነግሮናል፡፡ለማንኛውም ይሰጠውና አሰርቶ እውነቱን ይንገረን::

The post ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) “የኃይሌ ገብረሥላሴ የብሔራዊ ቡድኑን የማሰልጠን ጥያቄ ድጋፍ ያሻዋል” appeared first on Zehabesha Amharic.


በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ድል ቀንቷቸዋል። ከ1-5 ባለው ደረጃ በመካከላቸውም ጣልቃ አላስገቡም

$
0
0

ዛሬ ጠዋት በዱባይ በተካሄደ የማራቶን ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንድም በሴቶች ከአንድ እስከ ሶስት በማሸነፍ በድል ተንበሸበሹ::

በወንዶች ተስፋዬ አበራ 2ሰዓት04ደቂቃ ከ24 ማይክሮ ሰከንድ አንደኛ በመውጣት ሲያሸንፍ ፣ለሚ ብርሃኑ 2ኛ ፀጋዬ መኮንን 3ኛ በመውጣት አሸናፊ ሲሆኑ በሴቶች ደግሞ ትርፌ ፀጋዬ 2ሰዓት ከ19ደቂቃ ከ41ማይክሮ ሰከንድ አንደኛ በመውጣት ስታሸንፍ አማኔ በሪሶ ሁለተኛ መሰለች መልካሙ ሶስተኛ በመሆን አሽንፈዋል::

በዚህም ለአትሌቶቹ እንደየ ደረጃቸው በአጠቃላይ ወደ አንድ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሽልማት ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::

sport 12 sport 2

The post በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ድል ቀንቷቸዋል። ከ1-5 ባለው ደረጃ በመካከላቸውም ጣልቃ አላስገቡም appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ጀግኖች አትሌቶች በዱባይ ማራቶን 2016 ድንቅ ድል ተጎናጸፉ

$
0
0

ethiopians

ነቢዩ ሲራክ
ጥር 13 ቀን 2008 ዓም

======================================
* እንኳንም ደስ ያለን !
* ከወንዶች ተስፋየ ከሴቶች ትርፊን የቀደመ አልነበረም !

1000 የሚገመቱ ተሳታፊዎች በሚሳተፉበት ዘንድሮ በዱባይ እየተካሔደ ባለው የዱባይ ማራቶን 2016 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአረንጓዴውን ጎርፍ ድል በበርሃዋ የአረብ ኢምሬት ከተማ በዱባይ ደግመውታል ! አንጸባራቂውን ድል የደገሙት አትሌቶቻችን በወንድና በሴት በተደረገው ውድድር ተከታትለው በመግባት ያገኙት ውጤት በውድድሩ የበላይነትን አቀናጅቷቸዋል ።

በወንዶች አሸናፊ የሆነው ተስፋየ አበራ ዲባባ የገባበት ሰዓት 02:04:24 መሆኑ ታውቋል ። በሁለተኛነት ተስፋየን ተከትሎ የገባው የአምናው አሸናፊ ለሚ ብርሃኑ ኃይሌ 02:04:33 ሰዓት ሲያስመዘግብ በሶስተኛነት ጸጋየ መኮንን አሰፋ 2:04:46; ሰዓት ማስመዝገቡ ታውቋል ።

በሴቶች ውድድር አሸናፊ የሆነችው ትርፊ ጸጋየ ብየነ 02:18:41 ሰዓት ስታስመዘግብ አማኔ ብሪሶ ሻንኩሌ በ 02:20:48 ሰዓት በሁለተኛነት ገብታለች ። መሰለች መልካሙ ኃይለየሱስ በ02: 22:29 ሰዓት በሶስተኛነት ተከትላ መግበቷም ታውቋል !

በወንድም በሴትም በተደረገው ውድድር ከ1 እስከ 5 ተከታትለው የገቡበትን ሙሉው ውጤት እንደሚከተተለው ነው !

በወንዶች Men (All from Ethiopia)

1) Tesfaye Abera Dibaba – 2 hours: 04 minutes: 24 seconds;
2) Lemi Berhanu Hayle 2:04:33;
3) Tsegaye Mekonnen Asefa 2:04:46;
4) Sisay Lemma Kasaye 2:05:16;
5) Mula Wasihun Lakew 2:05:44.

በሴቶች Women (all from Ethiopia):

1) Tirfi Tsegaye Beyene 2:19:41;
2) Amane Beriso Shankule 2:20:48;
3) Meselech Malkamu Haileyesus 2:22:29;
4) Sutume Asefa Kebede 2:24:00;
5) Mulu Seboka Seyfu 2:24:24.

አስገራሚውን ድል በቦታው በመገኘት የታዘቡት በዱባይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለአትሌቶች ከፍ ታለ ሞራል ሲሰጡ መዋላቸው የአረብ መገናኛ ብዙሃምንን አትኩሮት በአድናቆት ስበውት ተስተውሏል !

እንኳን ደስ አለን !

The post Sport: ጀግኖች አትሌቶች በዱባይ ማራቶን 2016 ድንቅ ድል ተጎናጸፉ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ማንቸስተር ዩናይትድ ቫንገሃልን ለማሰናበት ከጫፍ ደርሷል |ተጫዋቾች አውራ ጣቶቻቸውን ዝቅ እያደርጉባቸው ነው

$
0
0

Van Gaal Louis
(ዘ-ሐበሻ) ሆላንዳዊው አሰልጣኝ ልዊስ ቫንገሃል ማን.ዩናይትድን ከተረከቡ በኋላ ባደረጉት 78 ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻሉት 31 ጊዜ ብቻ ነው:: 29 ጊዜ አቻ ሲወጡ 18 ጊዜ ደግሞ ባልተጠበቁ ቡድኖች ሳይቀር ተሸንፈዋል::

የማን. ዩናይትዱ አሰልጣን ቫንገል በተለይ ከቅዳሜው የሳውዝ ሃምፕተን ጨዋታ ሽንፈት በኋላ ከክለቡ ይሰናበታሉ የሚለውን መረጃ በፍጥነት እያስኬደው ይገኛል:: ተጫዋቾቹ በአሁኑ ወቅት የአሰልጣኙን የአጨዋወት መንገድ መከተል ማቆማቸውን የሚገልጹት መረጃዎች በክለቡ ውስጥ ለረጅም ጊዜያት የተጫወቱ ተጫዋቾች አውራጣታቸውን ዝቅ በማድረግ ለአሰልጣኙ ያላቸውን ተቃውሞ እያሳዩ ነው::

አንዳንድ ተጫዋቾች አሰልጣኙ እንዲሰናበቱ ለክለቡ ቺፍ ኤድ ውድ ዋርድ መናገራቸውን የሚገልጹት መረጃዎች ክልቡን ሙሉ በሙሉ ሪያን ጊግስ እንዲይዘው ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸው ተሰምቷል:: ኤድ ውድ ዋርድም ለማንቸስተር ዩናይትድ ያልተጠበቀ ሽንፈት ተጫዋቾች ለአሰልጣኙ አጨዋወት ዘዴ ደስተኛ ባለመሆናቸው መሆኑን መረዳታቸውን ከክለቡ የሚመጡ መረጃዎች ያመለክታሉ::

ቫንግሃል ከተሰናበቱ ሪያን ጊግስ ክለቡን ይህ ሲዝን እስከሚጠናቀቅ ሊመራው ይችላል የሚሉ ዘገባዎች ቢኖሩም ጊግስ ተጠባባቂ አሰልጣኝ ሳይሆን በቋሚነት መያዝ እንደሚፈልግ ተዘግቧል::

The post Sport: ማንቸስተር ዩናይትድ ቫንገሃልን ለማሰናበት ከጫፍ ደርሷል | ተጫዋቾች አውራ ጣቶቻቸውን ዝቅ እያደርጉባቸው ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ሊዮኔል ሜሲ የዓለማችን ምርጡ ተጫዋች

$
0
0

ከ2008 ወዲህ ባሉት ዓመታት የፊፋ ባሎን ደ ኦር ሽልማትን ሁለት ተጨዋቾችን ብቻ ማለትም ሊዮኔል ሜሲ እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ በየተራ ሲፈራረቁበት መዝለቃቸው ይታወሳል፤ ሆኖም ግን እስካሁንም ድረስ ከሁለቱ አርጀንቲናዊው የዓለማችን እጅግ ምርጡ ተጫዋች ማነው? የሚለው ጉዳይ መወያያ ርዕስ ሆኖ መዝለቁ አልቀረም፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የዓለማችን ምርጥ የፉትቦል ተንታኞች ሰሞኑን ካስነበቡት ፅሑፍ ውስጥ ግን ከዚህ በታች ያለው ሙያዊ ዳሰሳቸው የ26 ዓመቱ አርጀንቲናዊ የባርሴሎና ኮከብ መጠነኛ የሆነ ብልጫን መያዙን የሚጠቁም ሆኗል፡፡

mesi2

ባለፉት 10 ዓመታት ውስጥ የያዘውን ከፍተኛ ብቃትን በሜዳ ላይ እንዲወጣ በማስቻልና በዙሪያው ከሚገኙት የቡድን ጓደኞች በተገቢው መልኩ ተጠቃሚ በመሆን ብልህነቱ ሊዮኔል ሜሲ ከዋነኛ ተቀናቃኙ ክርስቲያኖ ሮናልዶ አንፃር የተሻለ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ዘልቋል ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በእርግጥ ሮናልዶ በ2014/15 ሲዝን በ54 ግጥሚያዎች ላይ 61 ጎሎችን ለማስቆጠር የቻለበት ሪከርዱን ሜሲ በተመሳሳይ የውድድር ዘመን በ57 ግጥሚያዎች 58 ጎሎን ለማስቆጠር ከቻለበት ሪከርዱ አንፃር የተሻለ የሚባል ነው፤ ሆኖም ግን አርጀንቲናዊው  ኢንተርናሽናል በ2015 ከባርሴሎና ጋር የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ድልን ለመቀዳጀት ከመቻልም አልፎ ለስፓኒሽ ላሊጋ ሻምፒዮንነትና ለኮፓ ዴል ሬይ ድሎችም መብቃቱ ሲታወስ የሚኖር አይነት ተደናቂ የውድድር ዓመትን ለማሳለፍ ችሏል፡፡ ሜሲ ከባርሴሎና ጋር የሶስትዮ ዋንጫ ድልን ሉዊስ ሱዋሬዝ እና ኔይማር ከጎኑ ሆነው ያበረከቱለት እገዛን ከፍተኛነት ችላ ሊባል የማይገባው ነው፡፡

ጋሬዝ ቤል፤ ሀሜስ ሮድሪጌዝ እና ካሬም ቤንዜማ ግን ለክርስቲያኖ ሮናልዶ የሰጡት ድጋፍ ያነሰ የሚባል ነው፡፡ ሪያል ማድሪድ በእያንዳንዱ የውድድር ዓመት ትልቅ ስም ያላቸው ተጫዋቾችን በስኳዱ የመያዝ ባህል ያለው ቢሆንም ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ2009 ፕራሲዝን ማንቸስተር ዩናይትድን በመልቀቅ ሳንቲያጎ በርናባው ከደረሰ ወዲህ ግን ከአንድ በላይ የስፓኒሽ ላ ሊጋ ሻምፒዮንነት ክብርን ለመቀዳጀት አልቻለም፡፡ ይህ በዚህ ወቅት አትሌቲኮ ማድሪድ ካስመዘገበው ሪከርዱ ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑም ሮናልዶ ከያዘው ትልቅ ደረጃ አንፃር በዙሪያው የሚገኙት ተጫዋቾችን ለዋንጫ ድሎች የማነሳሳት አስተዋፅኦን ከሊዮኔል ሜሲ አንፃር አነስተኛ የሚባል መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡

ሮናልዶ ከቡድኑ ጋር ከሚቀዳጃቸው የዋንጫ ድሎች ይልቅ በግሉ ለሚያገኛቸው ሽልማቶች ከፍተኛ የሆነ ጉጉት እንዳለውም በቅርቡ ባወጣው የራሱን ህይወትን የሚዳስስ ዶክመንተሪ ፊልም ላይ በሰጠውመግለጫ ያንፀባረቀ ሆኗል፡፡ በወቅቱ ፖርቹጋላዊው ኢንተርናሽናል በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየቱን የሰዘነረው ‹‹ከ2009 እስከ 2012 ድረስ ባሉት አራት ተከታታይ ዓመታት ሊዮኔል ሜሲ የባሎን ደ ኦር ሽልማትን ሲያገኝ ራሴን እንድወቅሰው ምክንያት ሆኖኝ ነበር የሚል ነው፡፡

ይህ የክርስቲያኖ ሮናልዶ አስተያየት እግር ኳስ የቡድን ስፖርት መሆኑን እስከመዘንጋት ደረጃ ደረሰ የመሰለበት ተደርጎ ተቆጥሮበታል፡፡ ሜሲን ከሮናልዶ በላይ የዓለማችን ትክክለኛው እጅግ ምርጡ ተጫዋች የሚያስብለውም ዋነኛው መስፈርት ለቡድን ስራ የሚሰጠው ከፍተኛ የሆነ ከበሬታ ነው፡፡ በ2015 ዓመት ሊዮኔል ሜሲ ለቡድን ጓደኞች የፈጠራቸው ጎሎችን የማስቆጠር እድሎች ሮናልዶ በተመሳሳይ ወቅት በስ ካስመዘገባቸው ጋር በጭራሽ የማይደራረስ መሆኑን የሚያንፀባርቅም ጭምር ነው፡፡ አርነጅቲናዊው ኮከብ በኢንተርናሽናል ደረጃም ከፖርቹጋላዊው አንፃር በብዙ መልኩ የሚሻል ሪከርድን በ2015 የውድድር ዓመት ለማስመዝገብ ለመቻሉ የአገሩ ዋናው ብሔራዊ ቡድንን በአምበልነት ለመምራት በቺሊ አዘጋጅነት በተካሄደው የኮፓ አሜሪካ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ ያደረሰበት በቂ ማስረጃ ነው፡፡ በዛ የፍፃሜ ግጥሚያ ሜሲ አርጀንቲናን ለዋንጫ ሽልማት ባለቤትነት ለማብቃት ያልቻለው ቡድኑ የመለያ ምቶች ዕድለቢስ ስለነበር እንደሆነ ይታወሳል፡፡

The post Sport: ሊዮኔል ሜሲ የዓለማችን ምርጡ ተጫዋች appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ‹‹የተከላካይ ክፍሉ በዚህ ጥንካሬው ከቀጠለ ዩናይትድ የውድድር ዘመኑን በስኬት የማጠናቀቅ ዕድሉ የሰፋ ነው›› ዳቪድ ደ ሂያ

$
0
0

 

ምንም እንኳን ማንችስተር ዩናይትድ ከሊጉ መሪ አርሰናል በዘጠኝ ነጥቦች ርቀት ላይ ቢገኝም የግማሽ የውድድር ዘመን የቀያዮቹ ሰይጣኖች አቅም ሲመዘን አሁንም ዩናይትድ የሊጉ ሻምፒዮን አሊያም በቻምፒዮንስ ሊግ የሚያሳትፈውን ደረጃ ይዞ ለማጠናቀቁ ዋስትና የለውም፡፡

David de Gea

ግብ ለማስቆጠር የሚቸገረው የሉዊ ቫን ሃል ቡድን በመጀመሪያው ሮክ ግማሽ የውድድር ዘመን ጥሩ ጎኑ ይነሳ ከተባለ የተከላከይ ክፍሉ በየጨዋታው በአማካይ ከአንድ ጎል በታች የሚያስተናግድበት መልካም ሪከርዱ ነው፡፡ ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ደ ሂያ አሁንም ምርጥ ብቃቱን ይዞ መዝለቁ ጉልህ ድርሻ አለው፡፡ ታዲያ ግብ ጠባቂው በውድድር ዘመኑ ዩናይትድ አንድ አይነት ዋንጫን አንስቶ ማጠናቀቅ ከፈለገ ይሄን የመከላከል ሪከርዱን ጠብቆ መጓዝ እንደሚኖርበት ሂያ በአፅንኦት ያስረዳል፡፡

በስፔን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የአኪር ካሲያስ የረዥም ጊዜ ተተኪ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ዳቪድ ደ ሂያ በሰጠው ቃለ ምልልስ ይሄንና ሌሎችን ጉዳዮች ዳስሷል፡፡

ጥያቄ፡- ተደጋጋሚ ጉቶች የፈጠረው ተፅዕኖ እንዳለ ሆኖ የጣላችኋቸው ቁልፍ ነጥቦች ተስፋ እንድትቆርጡ አድርጓችሁ ይሆን?

መልስ፡- ይመስለኛል፡፡ ሁልጊዜም ቁልፍ ተጨዋቾች ጉዳት የሚያስተናግዱ ከሆነ ጨዋታዎችን ማሸነፍ ይከብዳል፡፡ እኛም በዚህ አይነት ሁኔታዎች ያለፍንባቸው አጋጣሚዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ይሄ በተለይ ደረጃው ከፍ ባለ ሊግ የሚያጋጥም ነገር ነው፡፡ ኣዲሶቹ ወጣቶች ልምድ ያላቸውን ተጨዋቾች ተክተው የሚችሉትን ያህል አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ የአንጋፋዎቹን ያህል አስተዋፅኦ ከወጣቶቹ መጠበቅ ግን ተገቢ አይመስለኝም፡፡

ጥያቄ፡- ከዘንድሮው ዩናይትድ ጥሩ ነገር ይነሳ ከተባለ የተከላካይ ክፍሉ ሪከርድ ይጠቀሳል፡፡ በሙሉ ጥንካሬው ላይ ሲገኝ የውድድር ዘመኑን በስኬት ለማጠናቀቅ ምን ያህል አስተዋፅኦ ይኖረዋል?

መልስ፡- የተከላካይ መስመራችን ከአምናው በተሻለ ዘንድሮ ጠንካራ ይመስልሃል፡፡ ይሄ ደግሞ በጣም ወሳኝ እና አስፈላጊ ነው፡፡ ጎሎችን እንደ አምናው አብዝተን እያስተናገድን አይደለም፡፡ በማጥቃት ሚና ያለንን ጥራት በሚገባ ተጠቅመን ጎሎችን ካስቆጠርንና የተከላካይ ክፍሉ በዚህ ጥንካሬው ከቀጠለ ዩናይትድ የውድድር ዘመኑን በስኬት የማጠናቀቅ ዕድሉ የሰፋ ነው፡፡

ጥያቄ፡- ከዚህ ቀደም በኦልድ ትራፎርድ መጫወት የሚከብዳቸው በተለይ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ዩናይትድን እየፈተኑት ነው፡፡ ምናልባት የትኩረት እና የመደራጀት ችግር ይሆን?

መልስ፡- ይመስለኛል፤ ብዙ ጊዜ በኦልድ ትራፎርድ ስንጫወት ኳስን አብዝተን ስለምንቆጣጠር፤ በትኩረት ማጣት ጎሎችን አስተናግደን ነጥብ የጣልንባቸው ጨዋታዎች ነበሩ፡፡ አንዳንድ ቡድኖች ለረዥም ደቂቃ የጎል ዕድል ሳይፈጥሩ ቆይተው በድንገት መዳኛ መከላከል ቀጠና ይደርሳሉ፡፡ በዚህ ጊዜ የመከላከል ቅርፃችን ከተበላሸና ትኩረታችንን ካጣን ጎል ይቆጠርብናል፡፡

ጥያቄ፡- አንተ ወደ ኦልድ ትራፎርድ በመጣህበት ዓመት በሜዳችሁ ስትጫወቱ የነበረውን ሁኔታ ከዘንድሮው ጋር ስታነፃፅረው ምን አይነት ምስል ይሰጥሃል?

መልስ፡- ወደ ኦልድ ትራፎርድ መጥተው የሚጫወቱ ክለቦች ሁልጊዜም አዕምሯቸው ውስጥ የሚይዙት ከግዙፍ ክለብ ጋር እንደሚጫወቱ ነው፡፡ እነዚህ ክለቦች በራሳቸው ሜዳ ላይ ጥቅጥቅብለው መጫወትን ይመርጣሉ፡፡ ግን እንደ የክለቦቹ ይለያያል ክፍተቶችን ፈልገው ጎል ሊያስቆጥሩብን የሚመጡ ቡድኖችም ነበሩ፡፡ አሁን የዚህ አይነት ቡድኖች በርክተዋል፡፡

ጥያቄ፡- በማንቸስተር ዩናይትድ አምስተኛ ዓመትህን ይዘሃል፡፡ ከቆይታህ አንፃር አሁን የበለጠ ኃላፊነት ይሰማሃል?

መልስ፡- አሁን በዩናይትድ በርካታ አዳዲስ ወጣቶችን እየተመለከትኩ ነው፡፡ በርካታ ጨዋታዎችን ታደርጋለህ፡፡ ይሄ ደግሞ ተፅዕኖህ ከፍ እያለ እንዲሄድ ያደርገዋል፡፡ እንደ ግብ ጠባቂነቴ በተለይ የተከላካይ ክፍሉን መምራት ይጠበቅብኛል፡፡ ተከላካዮቻችን ከጫና ነፃ ሆነው እንዲጫወቱ ያደርጋቸዋል፡፡

ጥያቄ፡- በቻምፒዮንስ ሊግ ከምድብ ጨዋታዎች ማለፍ አለመቻላችሁ ምን ስሜት ፈጠረባችሁ? ዩሮፓ ሊግ መፅናኛ ይሆናችኋል?

መልስ፡- ዩሮፓ ሊግ ለእኔ ጥሩ ስሜት የሚሰጠኝ ፉክክር ነው፡፡ በተለይ በ2010 ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ሆኜ ይሄን ዋንጫ አጣጥሜዋለሁ፡፡ ነገር ግን ይሄ በቻምፒዮንስ ሊግ ታሪክ ደማቅ አሻራ ያለው ማንቸስተር ዩናይትድ ነው፤ አሁን በሌላ ውድድር ውሰጥ ነን፤ ዩሮፓ ሊግን በዜይቢያዊ መንገድ ለማሸነፍ ጥረት እናደርጋለን፡፡ የማክሰኞ እና ረቡዕ የቻምፒዮጀንስ ሊግ ምሽቶችን ለለመደው ዩናይትድ ግን እንግዳ ነገር መሆኑ እርግጥ ነው፡፡ ቢሆንም ግን የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎችን በበቂ ዝግጅት ማድረግ ይኖርብናል፡፡ የምንገጥመው ትንሽ የሚመስለውን የዴንማርኩን ሚዲቲላድን ነው፤ ነገር ግን የደርሶ መልሱን ጨዋታ አሸንፈን በድል መንገድ እንደምንጓዝ ሙሉ ተስፋ አለኝ፡፡

ጥያቄ፡- ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር የዩሮፓ ሊግን ዋንጫ ያነሳው ከቻምፒዮንስ ሊግ ውጭ ከሆናችሁ በኋላ ነበር፡፡ ድሉን ያከበራችሁት ግን ለየት ባለ ሁኔታ ነበር፡፡

መልስ፡- በጣም ትክክል፡፡ ዋንጫዎችን ማሸነፍ የተለየ ስሜት ይሰጣል፡፡ እግርኳስ የቡድን ስፐርት እንደ መሆኑ ደስታውን በጋራ ማጣጣም ልዩ ነው፡፡ ለእኔ ግን የእንግሊዙን ፉልሃም አሸንፈን ዋንጫውን ያነሳንበትን ቀን የማልረሳው ነው፡፡

ጥያቄ፡- ከፊትህ የዩሮ 2016 ሻምፒዮና ይጠብቅሃል፤ ከፈረንሳይ ጉዞ በፊት ምን እያሰብክ ነው?

መልስ፡- ውድድሩ የሚጀምረው ገና ሰኔ ወር ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው ከዚያ በፊት በርካታ ፈተናዎች በክለቤ ይጠብቀኛል፡፡ ጊዜው ሲደርስ ግን ልዩ ስሜት የሚፈጥር ውድድር ይሆናል፡፡ ከስሜን ጋር የዩሮ 2012 ክብራችንን ለማስጠበቅ ከቡድኑ ጋር ተካትቼ መጓዝ ያስደስተኛል፡፡

The post Sport: ‹‹የተከላካይ ክፍሉ በዚህ ጥንካሬው ከቀጠለ ዩናይትድ የውድድር ዘመኑን በስኬት የማጠናቀቅ ዕድሉ የሰፋ ነው›› ዳቪድ ደ ሂያ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: የአድናን ያንዩዣይ መመለስ  |ለማንቸስተር ዩናይትድ የሚያስገኙለት 5 ቁልፍ ጠቀሜታዎች

$
0
0

 

ቤልጂየማዊው ኢንተርናሽናል አድናን ያንዩዣይ የዘንድሮ ሲዝን የጀመረው ለማንቸስተር ዩናይትድ ጎል በማስቆጠር የታጀበ ጥሩ እንቅስቃሴን በማሳየት ቢሆንም በሆላንዳዊው አሰልጣኝ ሉዊ ቫንሃል ግን ከፒ ኤስ ቪ አይንደንሆቨን የገዙት ሜምፌስ ዴፓይን ውጤታማ ፉትቦልን ለማጉላት በመጓጓት ያንዩዣይን በውሰት ውል ወደ ቦሪሽያ ዶርትሙንዱ የመልቀቅ ውሳኔ ላይ ደርሰዋል፡፡ ያንን ውሳኔያቸውን በማስመልከት ቫንሃል በተደጋጋሚ በሰጡት መግለጫዎች ከጀርመን ቡንደስሊጋ ውድድር በመሳተፍ በቂ ልምድን አግኝቶ እንደሚመለስልኝ በመጓጓት ነው ቢሉም በተግባር ከታየው ለመረዳት ያስቻለው ግን የያንዣይ በውሰት ውል ማምረት ሶቱን አካሎች ማለትም ቦሪሽያ ዶትሙንድ ማንቸስተር ዩናይትድና ራሱ ተጫዋቹን ያልጠቀመ ሆኗል፡፡

januzai

ምክንያቱም ያንዩዣይ ለቦሪሽያ ዶርትሙድ የተሰለፈው በአራት ግጥሚያዎች ብቻ ነው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ብቻ የቡንደስሊጋ ግጥሚያው ነው ሌሎቹ ሶስት ጨዋታዎችን ያደረገው በዩሮፓ ሊግ ውድድር ነው፡፡ የዶርትሙንዱ አሰልጣኝ ለያንዣይ በበቂ ግጥሚያዎች የመሰለፍ እድልን ያልሰጡበት ምክንያት የሚገልኑት ግጥሚያዎችን ለማድረግ የስነ ልቦና ጥንካሬ አልታየበትም በማለት ነው፡፡

ይህ አባባላቸው በ20 ዓመቱ ቤልጅየማዊው ኢንተርናሽናል በቫንሃል ችሎታው ሙሉ እምነትን ባለማሳደሩ መጠነኛ የሆነ የመረበሽ መንፈስ እንደተፈጠረበት ነው ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ ግን ዶርትሙንድ የያንዩዣይን ለአንድ ዓመት የሚዘልቅ የውሰት ውልን ለማቋረጥ በመስማማት ሉዊ ቫንሃል ወደሚወደው ክለቡ ማንቸስተር ዩናይትድ መልሰውታል፡፡ ይህንን ተከትሎም የያንዩዣይ ወደ ኦልድትራፎርድ መመለስ ከጉዳቱ ይልቅ ጠቀሜታው የሰፋ እንደሚሆን በማመን አስተያየታቸውን የሚሰጡ ባለሙያዎች ተበራክተዋል፡፡ በተለይም የዛሬ ሁለት ዓመት ከማንቸስተር ዩናይትድ ፉትቦል አካዳሚ ወደ ዋናው ቡድን ለመሸጋገር የቻለው ቤልጅየማዊው ወጣት ወደ ኦልድትራፎርድ መመለሱ በአሁኑና በሲዝኑ መጨረሻ መካከል ለሉዊ ቫንሃል ቡድን የሚኖረውን ጠቀሜታዎችን የዴይሊ ሚረር የፉትቦል ተንታኞች ከዚህ በታች ባለው መልኩ ዘርዝረዋቸዋል፡፡

1. ጎል የማስቆጠር ተሰጥኦው

ማንቸስተር ዩናይትድ የዘንድሮን ሲዝንን ያጋመሰው ከዚህ በፊት በነበረው በተለይ ሁኔታ በበቂ ጎሎችን የማስቆጠር ረሃብ ተፈጥሮበት ነው፡፡  ለዚህ አንዱ ችግሩ የቡድኑ የአጥቂና አማካይ ክፍል ተጨዋቾች የጎል ማስቆጠር ሙከራዎችን የማድረግ ድርጊትን እያጡ ሲመጡ መታየታቸው ነው፡፡ ይህ ዥ ችግራቸው ማንቸስተር ዩናይትድ በእስካሁኑ ሲዝን ባደረጋቸው 20 የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች 24 ጎሎቹ ብቻ እንዲኖሩት መንስኤ ሆኖታል፡፡ ያንዩዣይ ግን በሚፈጠሩለት ጎል የማስቆጠር እድሎችን ካለምንም ማመንታት ለመጠቀም ከርቀት ሳይቀር ጠንካራ ሹትን በመምታት ከፍተኛ ድፍረትን የተላበሰ ተጨዋች ነው፡፡

2. የሚያስገኘው ከፍተኛ ፍጥነት

በሉዊ ቫንሃል ስር በማንቸስተር ዩናይትድ የማጥቃት እንቅስቃሴ በመታየት ላይ ያለው ችግሮች ውስጥ ከፍተኛ ፍጥነቱ በጣት አንዱ ነው፡፡ ይህንን ችግሩን ለመቅፈረፍ ሲሉም ቫንሃል በዘንድሮው ሲዝን ዝውውር መስኮት ፔድሮ ባርሴሎና ለመግዛት ተቃርበው ነበር፡፡ ሆኖም ግን ፔድሮ በመጨረሻው ሰዓት ወደ ቼልሲ ማምራትን ምርጫው በማድረጉ ጥረታቸው ሳይሰምርላቸው ቀርቷል፡፡ ከዚህ አንፃር ሌላው ከፍተኛ ፍጥነትን የተላበሰ የማጥቃት እንቅስቃሴ ያለው ያንዩዠይን የውሰት ውሉን አቋርጦ እንዲመለስ ባደረጉበት ውሳኔያቸው ፔድሮን ሲያስፈርሙበት የቀሩበት ስህተታቸውን መጠነኛ የሆነ እርምትን የሚያስገኙለት እንደሚሆን ይታመናል፡፡

3. በተጋጣሚ ላይ የሚፈጠረው ጫና

ያንዩዣይ በተፈጥሮው በተጋጣሚ ቡድን የተከላካይ መስመር ተሰላፊዎች ላይ የኳስ ቁጥጥርን ይዞ በመሮጥ ከፍተኛ ጫና እንዲፈጠርባቸው የማድረግ ተሰጥኦው ከፍተኛ ነው፡፡ ይህ ተሰጥኦው የክለቡ ደጋፊዎች በመነቃቃት ለቡድናቸው ለሙሉሃይሉ የማጥቃት ተነሳሽነት እንዲኖው የማያቋርጥ ድጋፍን እንዲሰጡት የሚያስገድዳቸው ይሆናል፡፡

ምክንያቱም ያንዩዣይ በከፍተኛ ፍጥነት የታጀበ ድሪብሊንጎችን በሚያደርግበት ወቅት በኦልድትራፎርድ ተደናቂ ድባብ እንዲፈጠር ምክንያት ሲሆን መታየቱ የተለመደ ነው፡፡

4. ለማን.ዩናይትድ ስኬት ያለው ተቆረቋሪነት

ሉዊ ቫንሃል ከተተቹበት ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ማንቸስተር ዩናይትድ በፉትቦል አካዳሚ ያፈራቸው ዳኒ ዌልቤክና ቶም ክሌቨርሌይን የመሳሰሉት የራሱ የሆኑ ተጨዋቾችን ወደ ሌሎች ከክለቦች እንዳይመሩ ያደረጉበት ተግባራቸው ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን ያንዩዣይን የመሰሉበት ተግባራቸው ከዚህ ወቀሳ ራሳቸውን ማዳን እንዲጀምሩ የሚረዳቸው እንደሚሆን ይታመናል፡፡

ደግሞም ቤልጅየማዊው ኢንተርናሽናል በማንቸስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች በከፍተኛ ደረጃ የሚፈቀር ለክለቡ ስኬታማነት ከፍተኛ የሆነ የተቆርቋሪነት መንፈስን በመላበስ በእያንዳንዱ ግጥሚያዎችን ከፍተኛ በሆነ በማሸነፍ ወኔ የማድረግ ባህል ያለው በመሆኑ ነው፡፡ የቤልጅየማዊው ከፍተኛ የማሸነፍ ወኔ በዙሪያው ላሉት የቡድኑ ጓደኞች በድል የመነሳሳትን መንፈስን የሚፈጥርላቸው እንደሚሆን ይታመናል፡፡

5. ለማታ የሚሰጠው ጠቀሜታ

ሉዊ ቫንሃል በስፔናዊው ኢንተርናሽናል ሁዋን ማታ ተደናቂ ኳሊቲዎችን በግራ ክንፍ በኩል እንዲሰለፍ በማስገደድ እያባከኑት ይገኛሉ፡፡ ምክንያቱም ለማታ ይበልጥ ተስማሚ የሚሆንለት ጨዋታ ሚና ከፊት አጥቂ ጀርባ ባለው ቦታ ወደመሃል ገብቶ የሚጫወትበት ነፃነትን የሚያገኝበት ነው፡፡ በአንፃሩ ያንዩዩይ የበለጠ ውጤታማ ግልጋሎትን የሚሰጠው በግራ ክንፍ በኩል ግጥሚያዎችን በመጀመር ወደ መሃል ሰንጥቆ በመግባት በጠንካራ ቀኝ እግሩ የጎል ማስቆጠር ሙከራዎችን የሚያደርግበት ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የያንዩዣይ መመለስ የማንቸስተር ዩናይትድ ግራ ክንፍን በመረከብ ወደ ማታ በሚመርጠው የጨዋታ ሚና በመሰለፍ ዕድልን ፈጠሮለት ነፃ እንዲወጣ የሚረዳው እንደሚሆን ይታመናል፡፡

 

The post Sport: የአድናን ያንዩዣይ መመለስ  | ለማንቸስተር ዩናይትድ የሚያስገኙለት 5 ቁልፍ ጠቀሜታዎች appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: አዲሱ መድፈኛ ሞሐመድ ኤልኔኒ ማነው?

$
0
0

 

አስተማማኝ የነበረው የፍራንሲስ ኮከለ እና የባንቲ ካቦርላ ጥምረት በጉዳት ሳቢያ መፍረሱን ተከትሎ አርሰን ቬንገር አሮን ራምሴን ከማቲው ፍላሚኒ ጋር ለመጫወት ተገድደዋል፡፡ ውድድር ዘመኑ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በደረሰበት ጊዜ መድፈኞቹ በጉዳት የመሳሳት አደጋ ቢጋረጥባቸውም የጥር ወር የዝውውር መስኮት ግን በጊዜ ደርሶላቸዋል፡፡

Mohamed Elney arsenal

አርሰናል የሊጉን ዋንጫ ከ12 ዓመታት በኋላ ለማንሳት መልካም አጋጣሚ እንደ ዘንድሮው ያገኘ አይመስልም፡፡ ታዲያ ይሄን ዕድል ለመጠቀም አርሰን ቬንገር ከዝውው ገበያው ሸምተዋል፡፡

ከእነዚህ ውስጥ በግንባር ቀደምትነት ሊጠቀስ የሚችለው የባዝሉ ሞሐመድ ኤልኔኒ የኤምሬትስን በር አንኳክቶ መግባቱ ነው፡፡ ገና የአምስት ዓመት ጨቅላ ሳለ ነው የታላቁን የግብፅ ክለብ አል አህሊን አካዳሚ የተቀላቀለው ኤልኒኔ ለአፍሪካ የምንጊዜውም ስኬታማ ክለብ ዋና ቡድን መጫወት ባይችልም ወደ አውሮፓ አቅንቶ በስዊዘርላንድ ከባዝል ጋር ጣፋጭ አምስት ዓመታትን አሳልፏል፡፡ በዝነኛው የሜዳ ቴኒስ ኮከብ ሮጀርስ ፌዴረር ከሚደገፈው ባዝል ጋር አራት የሊግ ዋንጫዎችን ማንሳት ችሏል፡፡ ኤልኔኒ ከባዝል ጋር የቻምፒዮንስ ሊግ ምሽቶችን አጣጥሟል፤ እንዲያውም በ2013 ቼልሲን ቢያሸንፍ የግብፃዊው አስተዋፅኦ ጉልህ ነበር፡፡

የ23 ዓመቱ አማካይ አሁን የመፈተኛ ጊዜው ላይ ደርሷል፡፡ በአርሰን ቬንገር የምልመላ ኔት ዎርክ አዲሱ መድፈኛ ለመሆን ችሏል፡፡ ቬንገር ለተንቃነቀባቸው የሆልዲንግ አማካይ ቦታ አይናቸው ብዙ አማትሯል፡፡ የስፖርቲንግ ሊዝበኑ ዊሊያም ካርቫልሆ፣ የሲቪያው ግሪጎርዝ ኪሪያ፣ ያክ እና የሳውዝምፕተኑን ቬክቶር ዋንያማ ትኩረታቸውን ከሳቡት መካከል ዋነኞቹ ነበሩ፡፡ በመጨረሻም ግን ሞሐመድ ኤልኒኔ ምርጫቸው ለመሆን በቅቷል፡፡ ለመሆኑ የአርሰናልን አማካይ ክፍል ጥንካሬ ይመልሳል የተባለለት ሞሐመድ ኤልኔኒ ጠንካራ ጎኑ የትኛው ነው? በቬንገር ይሞሉለታል ተብለው የሚጠበቁት ደካማ ጎኖቹስ? በየትኛውም ሚና ስታይል ስኬታማ ይሆናል?

የመጀመሪያው መንገድ

ኤልኔኒ የአል አህሊ አካዳሚን የተቀላቀለው እ.ኤ.አ በ1997 ነበር፡፡ ታዲያ የመኖሪያ ቤታቸው ከካይሮ ጥቂት ኪሎ ሜትሮች ርቃ ከምትገኘው ኤል ማሃላ ወደ አል አህሊ በየዕለቱ ወደ ልምምድ ለመሄድ በባቡር መጓዝ አልያም አውቶቡስ መሳፈር ይጠበቅበት ነበር፡፡ ጨቅላው ኤልኔኒ ይሄን ብቻውን ስለማይወጣው ወላጅ እናቱ ዘወትር አብረውት ይሆኑ ነበር፡፡

አመሻሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው መመለስም ግዴታቸው ነበር፡፡ በአል አህሊ ዕድገት ያሳየው ኤልኔኒ በወጣት ቡድን ደረጃ በግብፁ ኃያል ክለብ በርከት ያሉ ጨዋታዎችን ማድረግ ቢችልም ዋናውን ቡድን ሰብሮ ለመግባት ግን አልተቻለውም፣ እንዲያውም በ2008 አል አህሊ ለሌላኛው የግብፅ ክለብ ኤል ሞካውሉን አሳልፎ ሰጠው፡፡ በአዲሱ ክለቡ ወደ ዋናው ቡድን ለማደግ ሁለት ዓመታትን በትዕግስት ከጠበቀ በኋላ በግብፅ ሊግ በየሳምንቱ የሚታይ ፊት ሆነ፤ በብቃቱ የተማረኩ የግብፅ ከ23 ዓመት በታች ቡድን አሰልጣኝ ወደ ለንደን ኦሎምፒክ ባመራው የግብፅ ቡን ውስጥ አካተቱት፡፡ ግብፅ በሩብ ፍፃሜው በጃፓን ተሸንፋ ከኦሎምፒክ ውጪ እስክትሆን ድረስ ኤልኔኒ አራት ጨዋታዎች አደረገ፡፡

ኤልኔኒ በስዊዙ ባዝል እይታ ውስጥ የገባው ከለንደን ኦሎምፒክ በኋላ ነበር፡፡ ባዝል ለስድስት ወራት በኳስ አዘዋዋሪነት ብቃቱ አመርቂ ሆኖ ካገኘው በቋሚነት ሊያስፈርመው ከአል ሞካውሉን ጋር ስምምነት ላይ ደረሱ፡፡ በ2013 ባዝል የሊግ ዋንጫውን እንዳነሳ ኤልኔኒን በቋሚነት እንደሚያዘዋውረው ይፋ አደረገ፡፡

የአጨዋወት ስታይል እና ጥንካሬ

አብዛኛውን ጊዜ በጥልቅ አማካይነት ሲጫወት ቢስተዋልም በአማካይ ክፍል የተለያዩ ሚናዎችን በብቃት መወጣት ይችላል፡፡ ከሳጥን ሳጥን የሚሮጥ አማካይ ሆኖ ባዝልን አገልግሏል፡፡ ለአጥቂ ጀርባ የአስር ቁጥር ሚናን መወጣት እንደሚችልም አሳይቷል፡፡ ኤልኔኒ ረዥም ኳሶችን ለተጋጣሚዎቹ ሲያቀብል ስኬታማ ነው፡፡ የሚያስቆጥራቸው ጎሎች አብዛኞቹ ከፍፁም ቅጣት ምት ክልል ውጪ የተመቱ ናቸው፡፡ በቆሙ ኳሶች አጠቃቀሙ የሚወደሰው ኤልኔኒ የክለቡ ቋሚ የቅጣት ምት፣ ፍፁም ቅጣት ምትና የማዕዘን ምት መቺ ነው፡፡

የቴክኒክ ክህሎቱን ያህል ሜዳ ላይም አይደክሜ ነው፡፡ ኳሷን ለማስጣል የሚወርዳቸው ሸርተቴዎች በአብዛኛው ስኬታማ ናቸው፡፡ ባዝል ዘንድሮ በዩሮፓ ሊግ ስኬታማ ጉዞን ሲያደርግ ኤልኔን በአምስት ጨዋታዎች ከጥልቅ አማካይ ሚናው እየተነሳ ሁለት ጎሎችን አስቆጥሯል፡፡ የጨዋታ ኮከብ በተባለበት የፊዮረንቲና ጨዋታ ያስመዘገበው የማቀበል ስኬቱ 92.4 በመቶ ነበር፡፡

arsenal Mohamed

ደካማ ጎን

የበርካታ ኳሊቲዎች ባለቤት የመሆኑን ያህል ኤልኔኒ ድክመቶችም አሉበት፣ የድሪብል ችሎታውን ካላሳደገ በተለይ ተጭነው (higher up the pltch) የሚጫወቱ ቡድኖች ሲያጋጥሙት ይቸገራል፡፡ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ high tempo pressing አጨዋወት እየተመረጠ መምጣት ለኤልኔኒ ስጋት ሊሆን ይችላል፡፡

በአርሰናል የትኛው ሚና ይስማማዋል?

ሳንቲ ካዞርላ፣ ፍራንሲስ ኮከለ እና ጃክ ዊልሽር ከጉዳታቸው ሲያገግሙ የአርሰናልን የአጨዋወት ክፍል ጥንካሬ የመመለስ ብቃት ቢኖራቸውም፣ መድፈኞቹ ዕድሜያቸው የገፋው ሚኬል አርቴታ ቶማስ ሮዚስኪ እና ማቲው ፍላሚኒን በክረምቱ ኮንትራታቸው ሲጠናቀቅ ተሰናባቾች ናቸው፡፡

ኤልኔኒ ለአርሰናል የረዥም ጊዜ መፍትሄ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ካዞርላና ኮከለ ከጉዳት እስኪያገግሙ ለአርሰናል አማካይ ክፍል በቂ ሽፋን መስጠት ይችላል፡፡ በአማካይ ክፍል የተለያዩ ሚናዎች የመወጣት ኳሊቲ ቢኖረውም አርሰን ቬንገር በዋነኛነት በተከላካይ አማካይ ሚና የፍራንሲስ ኮክለ ሽፋን እንዲሆንላቸው ይፈልጋሉ፡፡

ባለፈው ሐምሌ ወር 23ኛ ዓመቱን የያዘው ኤልኔኒ ከፊቱ ብሩህ ጊዜ ይጠብቀዋል ብሎ መናገር ይቻላል፡፡ ወጣቶችን በማፍራት በሚታወቁት አርሰን ቬንገር እጅ መውደቁ ወደፊት የተሻሻለው እና ምርጡን ሞሐመድ ኤልኔኒን እንድናየው ያደረገን ይሆናል፡፡ ሞሐመድ ኤልኔኒ ከባዝል ወጥቶ ፕሪሚየር ሊጉን የተቀላቀለ ብቸኛው ግብፃዊ አይደለም፡፡ እንደ ወንድሙ የሚያየው እና በግብፅ በኤል ሞካውሉን ክለብ አብሮት የተጫወተው ሞሐመድ ሳላህም ለቼልሲ ተጫውቷል፡፡ ሳላህ በ2012 ባዝልን ሲቀላቀል ‹‹ወንድሙ›› ኤልኔኒ በዓመቱ ተከትሎታል፡፡

 

 

The post Sport: አዲሱ መድፈኛ ሞሐመድ ኤልኔኒ ማነው? appeared first on Zehabesha Amharic.


Sport: ባስቲያን ሽዌንስታይገር ‹‹ማንቸስተር ዩናይትዶች በመሆናችን በእስካሁኑ የተሻለ ስኬት ሊኖረን ይገባል››

$
0
0

 

schweinsteiger

በኪንግስ ፓወር ስቴድየም ቅዳሜ ምሽት በሌሲስተር ሲቲና በማንቸስተር ዩናይትድ መካከል በተደረገው የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች የተቆጠሩበት ጎሎች ለሁለት ተጨዋቾች የየራሳቸው የሆኑ አዳዲስ ታሪክን ለማስመዝገብ የቻሉባቸው ሆነዋል፡፡ የመጀመሪያው የ23 ዓመቱ እንግሊዛዊ አጥቂ ጃሚ ቫርዲ ለ11ኛ ተከታታይ የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያው ጎል በማስቆጠር ከዚህ በፊት በማንቸስተር ዩናይትዱ ዝነኛ ጎል አዳኝ ሩድ ቫንኒስተልሮይ በ2003 በአስር የሊጉ ግጥሚያዎች በተከታታይ ጎሎችን በማስቆጠር ይዞት የነበረው ከ12 ዓመታት በላይ የዘለቀውን ሪከርድ የሰበረበት ነው፤ ሌላኛው ደግሞ ጀርመናዊው ኢንተርናሽናል ባስቲያን ስዌንስቲገር በ2015 ፕራሲዝን ዝውውር መስኮት ባየር ሙኒክን በመልቀቅ ለማንቸስተር ዩናይትድ ከፈረመ ወዲህ ለአዲሱ ክለቡ ለመጀመሪያ ጊዜ ጎል ያስቆጠረበት ግጥሚያ መሆኑ ነው፡፡ በኪንግስ ፓወር ስቴዲየም በተደረገው ግጥሚያ ጃሚ ቫርዲ በጨዋታው 24ኛ ደቂቃ ላይ 11ኛዋን የፕሪሚየር ሊግ ጎሉን ከመረብ በማሳረፍ ሌሲስተር ሲቲን 1ለ0 በሆነ ውጤት በመምራት እንዲጀምር ቢያስችለውም እረፍት ከመውጣታቸው በፊት ሽዌንስቲገር የዳሊ ብሊንድ የመዓዘን ምት በግንባሩ በመግጨት የማንቸስተር ዩናይትድን የአቻነት ጎል ከመረብ አገናኝቷል፡፡

 

ከማንቸስተር ዩናይትድ በሁለተኛው ግማሽ የታየችው ብቸኛዋ ኢላማዋን ያገኘች ጎል የማስቆጠር ሙከራንንም ሽዌንስቲገር አድርጎ በሌሲስተር ሲቲው ግብ ጠባቂ ካስፐር ሽማይክል ተመልሳበታለች፤ ሆኖም ግን ሽዌንሲቲገር ከግጥሚያው መጠናቀቅ በኋላ በሰጠው መገለጫ በማንቸስተር ዩናይትድ ተጨዋችነቱ የመጀመሪያ ጎሉን በማስቆጠሩ ከመደሰት ይልቅ በተመዘገበው የአቻ ውጤት ማዘኑን በማረጋገጥ ለሌሎች የቡድኑ ጓደኞቹ በአርአያነት የሚጠቀስ አስተያየት ሲሰነዝር ተደምጧል፡፡

‹‹ቡድናችን ሙሉ ሶስት ነጥቦችን በማስመዝገብ የፕሪሚየር ሊግ ሰንጠረዥ የመሪነት ስፍራን መቆጣጠርን በማድረግ እንደመሆኑ ከግጥሚያው አንድ ነጥብ ብቻ መጋራታችንን እንደ መጥፎ ውጤት ቆጥሬዋለሁ›› በማለት ለማንቸስተር ዩናይትድ ቲቪ መግለጫውን መስጠት የጀመረው የ31 ዓመቱ ጀርመናዊ አማካይ በመቀጠልም ‹‹አብዛኛውን የጨዋታ ክፍለ ጊዜ የሳለፍነው ሰፊ የኳስ ቁጥጥርና ከፍተኛ የጨዋታ የበላይነትን በመያዝ እንደመሆኑ ብዛት ያላቸው ጎሎችን የማስቆጠር ዕድሎችን ለመፍጠር መቻል ነበረብን፣ ይህንን ኃላፊነታችንን በአግባ ለመፈፀም አለመቻላችን በግጥሚያው በቡድናችን የታየው ትልቅ አሳዛኝ አጋጣሚዎችን መሆኑን አምናለሁ፡፡ ወደ ሌሲስተር ሲቲ ሜዳ የመጣነው የማንቸስተር ዩናይትድ ተጨዋች ሆነን በመሀላችን ከእንደዚህ አይነቱ ሙሉ ሶስት ነጥቦችን የማግኘቱ ኃላፊነታችንን በአግባቡ  መፈፀም መቻል ነበረብን፡፡ በእርግጥ የሌሲስተር ሲቲ ተጨዋቾች አብዛኛውን ክፍለ ጊዜን ከራሳቸው የሜዳ ክልል ሳይወጡ በጠንካራ ሁኔታ የመከላከል ተግባርን መፈፀማቸው በቂ ክፍተትን እንድናገኝ ትልቅ ተፅዕኖን የፈጠረብን ሆኗል፡፡ ግን በሌሎች ግጥሚያዎች እንደዚህ አይነቱ በጠንካራ ሁኔታ የመከላከል ተግባራቸው የሚጠብቁን መሆኑን አምነን ተጋጣሚያችንን ለማስከፈት በዚህ ግጥሚያ ካሳየነውም በበለጠ የተቻለንን ሁሉ ከፍተኛ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል›› የሚል አስተያየቱን አክሏል፡፡

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን አምበል ሽዌንሲቲገር ለማንቸስተር ዩናይትድ ነጥቦችን የማስገኘት ተግባርን ሲፈፅም በሁለት ተከታታይ የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከአንድ ሳምንት በፊትም ማንቸስተር ዩናይትድ ዋትፎርድን 2ለ1 በረታበት የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ ሁለተኛዋን የማሸነፊያ ጎል ትሮይ ዴልኒ በስህተት በራሱ መረብ ላይ ለማሳረፍ እንዲገደዱ ምክንያት የሆነች ጎል የማስቆጠር ሙከራን አድርጎን ነበር፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ ሽዌንሲቲገር በመቀጠል አስተያየቱን የሰነዘረው ‹‹በማንቸስተር ዩናይትድ ተጨዋችነቴ ለመጀመሪያ ጊዜ በስሜ ያስመዘገብኳት ጎል በሌሲስተር ሲቲ ላይ ያስቆጠርኳት ነች፡፡ ለዚህ ክለብ የመጀመሪያዬ ጎል በመሆኗም አስደስታኛለች፣ ሆኖም ግን ደስታዬ የተሟላ ይሆን የነበረው ግጥሚያውን በሙሉ ሶስት ነጥቦች ለማጠናቀቅ ብንችል ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር ለማንቸስተር ዩናይትድ የበለጠ ወሳኝ ተግባርን ፈፅሜያለሁ የምለው ዋትፎርድን ለመርታት በቻልንበት ግጥሚያ ለ2ኛዋ ጎል መገኘት የፈፀምኩትን ነው፡፡ ምክንያቱም ለማንቸስተር ዩናይትድ ካስቆጠርኳት የመጀመሪያዋ ጎሌ ይልቅ የቡድናችን ሙሉ ሶስት ነጥቦችን ማግኘትን እመርጥ ነበር›› በማለት ነው፡፡

በሌሲስተር ሲቲ በተደረገው ግጥሚያ ከማንቸስተር ዩናይትድ ተጨዋቾች ውስጥ የበለጠ ውጤታማ የጨዋታ እንቅስቃሴን ማሳየት ችሏል በሚል በበርካታ የፉትቦል ተንታኞች አድናቆትን ያተረፈው ሽዌንስቲገር ቡድናቸው ሌሲስተር ሲቲን በራሱ ሜዳ ለማሸነፍ በጠንካራ ሁኔታ ዝግጅቱን ሲሰራ መዝለቁን በማረጋገጥ በሰነዘረው አስተያየት ‹‹የሌሲስተር ሲቲ የዘንድሮ ሲዝን አቋም እጅግ ጠንካራ መሆኑን ከግንዛቤ በማስገባት ሙሉ ትኩረትን ሰጥተን ጠንካራ ዝግጅት ስንሰራበት የከረምነው ጨዋታ ነው፡፡ በተለይም ጃሚ ቬርዲ አደገኛ የማጥቃት እንቅስቃሴ ያለው ተጨዋች መሆኑን ከማመን በምን መልኩ እንደምንቆጣጠረው ዝግጅት ስንሰራ ዘልቀናል፡፡ ሆኖም ግን በዚህ ግጥሚያ በከፍተኛ ፍጥነት በታጀበ የካውንተር አታክ ጎል ሲያስቆጥርብን ታይቷል፡፡ ይህ ከእስካሁኑ ሲዝን በብዙ መልኩ በበለጠ በሜዳ ላይ ላለው ፉትቦላችን ሙሉ ትኩረትን የመስጠት ኃላፊነት እንዳለብን ሊያረጋግጥልን የሚገባ ጉዳይ ነው›› በማለት ነው፡፡

በቅዳሜ ምሽቱ ግጥሚያ ከማንቸስተር ዩናይትድ በኩል ከሽዌንስቲገር ጥሩ አቋም ባሻገር አንድ ሊጠቀስ የሚገባው መልካም ነገር ሆላንዳዊው አሰልጣኝ የዛሬ ዓመት በኪንግስ ፓወር ስቴዲየም በሌሲስተር ሲቲ 5ለ3 ከተሸፉበት የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ ትልቅ ትምህርትን ማግኘታቸው ነው፤ ምክንያቱም ቫንሃል የአሁኑ ግጥሚያን ሌሲስተርን 3-5-2 የጨዋታ ፎርሜሽንን በማመሳሰል መጀመራቸው ከጃሚ ቬርዲ ጎል በስተቀር በቡድናቸው የተከላካይ መስመር ላይ የዛሬ ዓመት እንደነበረው አይነት ከፍተኛ ጫና እንዳይፈጠርባቸው የረዳቸው ሆኗል፡፡ ሉዊ ቫንሃል ቡድናቸው ከሌሲስተር ሲቲ ጋር 1ለ1 ከተለያዩበት ግጥሚያ በኋላ የሰጡት ፖስት ማች ፕሬስ ኮንፈረንስ ከዚህ በታች ያለው ነው፡፡

ሉዊ ቫንሃል በግጥሚያው ስለ ተመዘገበው ውጤት

‹‹በሌሲስተር ሲቲ ሜዳ ነጥብ መጋራታችን የሚያስፀፅት ሆኖብኛል፤ ምክንያቱም በግጥሚያው 90 ደቂቃዎች ውስጥ በአብዛኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ የበላይነትን የያዝንበት የጨዋታ እንቅስቃሴን አሳይተናል፡፡ ሆኖም ግን የመጨረሻው እጣ ፈንታችን በድል ማጠናቀቅ የሚገባንን ግጥሚያን 1ለ1 በሆነ ውጤት ለማጠናቀቅ መገደድ ሆኗል፡፡ ከግጥሚያው መጀመር በፊትና በእረፍት ሰዓት ለቡድናችን ተሰላፊዎች የሰጠኋቸው መመሪያ ለእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮንነት ክብር ለመብቃት የምንጓጓ ከሆነ እንደዚህ አይነቶቹ ግጥሚያዎችን የማሸነፍ ትልቅ ኃላፊነት አለብን ብያቸዋለሁ፡፡ በግጥሚያው ግን በበቂ ሁኔታ ጎሎን የማስቆጠር እድል ሳይኖራቸው ቀርቷል፡፡

ስለ ጃሚ ቬርዲ የመሪነት ጎል

‹‹የሌሲስተር ሲቲ ትልቁ ጠንካራ ጎን በረጅም ፓስ የመጣ ኳስን በአግባቡ በመጠቀም እንደዚህ አይነቱ ጎልን ማስቆጠር በመሆኑ ይህንን ለመቋቋም በልምምድ ወቅት ትኩረትን ሰጥተን መስራት ነበረብን፡፡ ይህንን ተግባርን ስንፈፅም ከርመናል፤ ሆኖም ግን ከሌሲስተር ሲቲ የመዓዘን ምት የተመለሰች ኳስን በማይታመን አይነት ከፍተኛ የካውንተር አታክ ሲስተም በመምጣት ጎሏን ሊያስቆጥሩብን ችለዋል፡፡ ጎሏ እንድትቆጠር የቡድናችን ተሰላፊዎች በተሻለ ሁኔታ የመከላከል ተግባርን በመፈፀም የጃሚ ቬርዲ አደገኛ የማጥቃት እንቅስቃሴን ሊቋቋሙት ይገባ ነበር፡፡

ይህንን ስል ግን ቬርዲ ጎሏን ለማስቆጠር ያደረገው በከፍተኛ ፍጥነት የታጀበ የማጥቃት እንቅስቃሴ ኳሊቲው ሊደነቅ እንደሚገባ በማመን ነው፡፡ የሌስተር ሲቱ የመዓዘን ምትን በተደራጀ የመከላከል ተግባር ለመቋቋም ከቻልን በኋላ ወዲያውኑ መረባችን በጎል ማስፈራችን አሳዛኝ ሆኖብኛል፡፡ ምክንያቱም ጎሏ የተገኘችው ተጨዋቾቹ ትልቁን ኃላፊነታቸውን ከፈፀሙ በኋላ ወዲያውኑ ነው››

ቡድናቸው የቆሙ ኳሶች ብቃቱን ስለማሳደጉ

‹‹ከቆሙ ኳሶች የማጥቃት እንቅስቃሴያችን ከዚህ በፊት ከነበረው አንፃር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተሻለ ሊሆንልን የቻለበት አንዱ ምክንያት ቅጣት ምቶችን የሚመቱልን ተጨዋቾች ብቃት አስተማማኝ ደረጃ ላይ መገኘቱ ነው፡፡ በሳምንቱ አጋማሽ ኮፒ ኤስ ቪ አይንድሆቨን ጋር ባደረግነው የቻምፒዮንስ ሊግ ግጥሚያም ዳሊ ብሊንድ በመአዘን ምት በትክክለኛው ቦታ ላይ ባስቲያን ሽዌንሲቲገርን ለማግኘት በመቻሉ የአቻነቷን ጎል እንድናገኝ ምክንያት ሆኖናል፡፡ የቆሙ ኳሶችን የሚመቱት ተጨዋቾችን ከአንዱ ግጥሚያ ወደ ሌላው በተሸጋገርን ቁጥር የመቀያየር ስትራቴጂ መያዛችንም ከዚህ መስፈርት ያለን ብቃት የተሻለ እንዲሆንልን ሌላኛው ምክንያት ሆኖናል፡፡

ቡድናቸው በርካታ እድሎችን ስላልፈጠረበት ጉዳይ

‹‹ይህንን ችግራችንን መቅረፍ ከቻልን ሁልጊዜም ሙሉ ትኩረትን ሰጥተን እየሰራንበት ያለው ጉይ መሆኑን ለማረጋገጥ እወዳለሁ፡፡ በዚህ ግጥሚያ ግን በምንመኘው መልኩ በበቂ ሁኔታ ጎል የማስቆጠር እድሎችን ለመፍጠር ሲሳነን ታይቷል፡፡ ለዚህ አንዱ ምክንያት የሌሲስተር ሲቲ ተጨዋቾች አብዛኛውን የጨዋታ ክፍለ ጊዜን ከራቸው የሜዳ ክልል ሳይወጡ ማሳለፋቸው የፈጠረብን ተፅዕኖ  መሆኑን ግን አምናለሁ፡፡ ተስፋ የማደርገውም ከፊታችን ካሉት ግጥሚያዎች በርካታ ጎል የማስቆጠር እድሎችን ለመፍጠር ያልቻልንበት ችግራችንን በአግባቡ ለመቅረፍ እንችላለን ብዬ ነው››

ዋይኒ ሩኒን ስለቀየሩበት ውሳኔያቸው

‹‹በሁለት የተለያዩ ምክንያቶች የደረስኩበት ውሳኔ ነው፡፡ የመጀመሪያው መጠነኛ የሆነ የህመም ስሜት ሊፈጠርበት በመቻሉ ነው፡፡ በሜዳ ውስጥ ሲያነክስም ታይቷል፡፡ ሁለተኛው ምክንያቴ ደግሞ በፊት አጥቂ መስመራችን በተጋጣሚ ቡድን የተከላካይ መስመር ጀርባ በከፍተኛ ፍጥነት የሚገባ ተጨዋችን ለማግኘት የምንችልበት የስትራቴጂያዊ ለውጥ ስላስፈለገኝ መሆኑን ለማረጋገጥ እወዳለሁ››

The post Sport: ባስቲያን ሽዌንስታይገር ‹‹ማንቸስተር ዩናይትዶች በመሆናችን በእስካሁኑ የተሻለ ስኬት ሊኖረን ይገባል›› appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ዋይኒ ሩኒ –ወደ ቀድሞ ወርቃማ ዘመኑ ይመለስ ይሆን?

$
0
0

 

የማንችስተር ዩናይትድ ጎሎችን ያለማስቆጠር ችግር የዘንድሮው ሲዝን መሰረታዊ ችግሩ ሆኖ እስካሁንም ድረስ ዘልቋል ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ቅዳሜ በኦልድ ትራፎርድ የዝቅተኛ ዲቪዚዮኑ ሼፊልድ ዩናይትድን 1ለ0 በረታበት የኤፍ ኤ ካፕ 3ኛ ዙር ግጥሚያም በዘንድሮው ሲዝን ለስምንተኛ ጊዜ 0ለ0 በሆነ ውጤት በመለያየት እስከመቃረብ ደረጃ ደርሶ ነበር፡፡

roney body kick

በግጥሚያው የማንችስተር ዩናይድ የመጀመሪያውን ኢላማ ያገኘች ጎል የማስቆጠር ሙከራን ለማየት እስከ 69ኛው ደቂቃ ድረስ ለመታገስ መታየቱንም ምን ያህል በቫንሃል ስር የማንቸስተር ዩናይትድ የማጥቃት ስትራቴጂ መላላቱን የሚያሳይ ነው፡፡ ከዚህ በፊትም ማንቸስተር ዩናይትድ በዝቅተኛ ዲቪዚዮኑ ሚድልስብራ ተሸንፎ ከካፒታል ዋን ውድድር ውጪ ለመሆን የተገደደው ሙሉውን 90 ደቂቃዎችን አንድ ጎልን እንኳን ለማስቆጠር ተስኖት ለማሳለፍ ሲገደድ በመታየቱ መሆኑ ይታወሳል፡፡

ያንን ችግራቸውን ለመቅረፍ ሲሉ ቫንሃል በቅዳሜው የኤፍ.ኤ.ካፕ ግጥሚያ የዋናው ቡድናቸው መደበኛ ቋሚ ተሰላፊዎች ይዘው ወደ ሜዳ ቢገቡም ከሼፊልድ ዩናይትድ ጋር የማሸነፊያ ጎልን ለማስቆጠር በባከነ 6 ደቂቃዎች ጭማሪ ውስጥ ዋይኒ ሩኒ በፍፁም ቅጣት ምት ነው፡፡ በ93ኛው ደቂቃ ላይ የዕለቱ አርቢትር ለማንቸስተር ዩናይትድ የፍፁም ቅጣት ምት እድልን የሰጡት ተቀይሮ በገባው ሆላንዳዊው ኢንተርናሽናል ሜምፊስ ዴፓይ ላይ በተሰራ ፋውል ነው፡፡

ከዚህ በተረፈ ግን አጠቃላዩ የማንቸስተር ዩናይትድ የማጥቃት እንቅስቃሴ ቡድኑ ጎሎችን ለማስቆጠር እንዲችል የሚረዳው አይነት አይደለም፡፡ ቫንሃል የቡድናቸው ጎል የማስቆጠር ችግርን ለመቅረፍ በጨዋታው 2ኛው ግማሽ የወሰዱት እርምጃም ከቡድናቸው በመከላከል ላይ ያተኮረ የጨዋታ እንቅስቃሴ ካላቸው ባስቲያን ሼዌንስቲገር እና ማሩዋን ፌላይኒ ይልቅ ሁዋን ማታ እና አንደር ሄሬራን ቀይረው በማስወጣት መሆኑ ከራሳቸው ክለብ ደጋፊዎች የተቃውሞ ድምፅ ተሰምቶባቸዋል፡፡

በዕለቱ ደካማ የጨዋታ እንቅስቃሴ የነበረው ቤልጅየማዊው ኢንተርናሽነል ማሩዋን ፌላይኒን ቀይረው ያስወጡት ዘግይተው መሆኑም ሌላው የተተቹበት ጉዳይ ሆኗቸዋል፡፡ በአጠቃላይም በግጥሚያው የማንቸስተር ዩናይትድ ብቸኛው የምስራች የቡድኑ አምበል ዋይኒ ሩኒ በሁለት ተከታታይ ግጥሚያዎች የማሸነፊያ ጎልን ለማስቆጠር መቻሉ ብቻ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡

ምክንያቱም ሩኒ የማንቸስተር ዩናይትድ የመጨረሻው የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያው ስዋንሲ ሲቲን 2ለ1 የረታበትን የማሸነፊያ ጎልንም ለማስቆጠር ችሏል፡፡ ሉዊ ቫንሃል ቡድናቸው ሼፊልድን 1ለ0 በማሸነፍ የኤፍ.ኤ.ካፕ ዘመቻውን ወደ 4ኛው ዙር ለማሸጋገር ከቻለ በኋላ በሰጡት ፖስት ማች ፕሬስ ኮንፈረንስ ውስጥ ከዚህ በታች ያለው ይገኝበታል፡፡

ስለ ቡድናቸው የጨዋታ እንቅስቃሴ

‹‹በመጀመሪያው ግማሽ በምንመኘው መልኩ በከፍተኛ ፍጥነት የታጀበ የጨዋታ እንቅስቃሴ ሳይኖረን ቀርቷል፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍ በክንፍ በኩል በተሻለ ሁኔታ የማጥቃት እንቅስቃሴን ማድረግ ነበረብን፡፡ በ2ኛው ግማሽ በተሻለ ሁኔታ ጎሎችን የማስቆጠር እድሎችን ለመፍጠር ችለናል፡፡ ሆኖም ግን የሼፊልድ ዩናይትድ ተሰላፊዎች በጠንካራ ሁኔታ ቅንጅትን ፈጥረው ሲንቀሳቀሱ በመታየታቸው በምንመኘው መልኩ በበቂ ሁኔታ የመከላከል ስትራቴጂያቸውን ለማስከፈት ሲሳነን ታይቷል››

ስለ ማሸነፊያዋ የፍፁም ቅጣት ምት

‹‹በእኔ አመለካከት ትክክለኛነት ያለው የፍፁም ቅጣት ምት እድልን ለማግኘት ችለናል፡፡ ደግሞም ሜምፊስ ዴፓይ ወደ ተጋጣሚያችን ፔናሊቲ ቦክስ በከፍተኛ ፍጥነት ሆኖ በመግባት ላይ በመሆኑ ጎል የማስቆጠር መልካም አጋጣሚን ሲከላከል ታይቷል፡፡ እሱ ግጥሚያውን ለማሸነፍ እንድንችል የረዳን የቡድናችን ትክክለኛው ጀግና ሆኗል ለማለት እችላለሁ፡፡ ከግጥሚያው በፊት ለቡድናችን ተላፊዎች የነገርኳቸው ነገር ከሁሉም ከፍተኛ ወሳኝነት ያለው ጉይ የኤፍ.ኤ.ካፕ ዘመቻችንን ወደ 4ኛ ዙር ለመሸጋር መቻላችንን ነው በሚል ነው፡፡ ባሰብነውም መልኩ ግጥሚያውን በድል ለማጠናቀቅ በመቻላችን በተመዘገበው ውጤት የማንደሰትበት ምክንያት አይኖርም››

rooney

ቡድናቸው ማሻሻል ስለሚገበው ብቃት

‹‹የጎል ማስቆጠር ዕድሎችን የመፍጠር ብቃቶችን ማሳደግም እስካሁንም ድረስ በልዩ ትኩረት ልንሰራበት የሚገባን ተግባር ነው፡፡ ለዚህ ተግባራዊነት የኳስ ቁጥጥሮችን በፍጥነት ወደ ፊት የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት ከፊታችን ይጠብቀናል፡፡ ይህንን ስል ቢያንስ ከእዚህ ግጥሚያ የሼፊልድ ዩናይትድ ተሰላፊዎች በጠንካራ ሁኔታ የመከላከልን ተግባር ለመፈፀም መወሰናቸው ግን ትልቅ ችግርን እንዲፈጠርብን መንስኤ ይሆናል››

ስለ ዋይኒ ሩኒ የፍፁም ቅጣት ምት

‹‹በግጥሚያው ይዣቸው የገባሁት የመጀመሪያዎቹ ሁለት የፍፁም ቅጣት ምት መቺዎች ሁዋን ማታ እና አንደር ሄሬራ ናቸው፡፡ ሆኖም ግን ሁሉንም ቀይሬ በማስወጣቴ ዋይኒ ሩኒ ፔናሊቲውን የመምታት እድለኛ ሊሆን ችሏል፡፡ ያለፉት ሁለት ግጥሚያዎቻችን ላይ በእያንዳንዱ የማሸነፊያ ጎልን ለማስቆጠር መቻሉም በራስ የመተማመን መንፈሱ እጅግ ያማረ ሁኔታ ላይ መገኘት መቻሉን የሚያሳይ ነው፡፡ ተስፋ የማደርገውም ከፊታችን ባሉት ግጥሚያዎች ላይ ሌሎች በርካታ ጎሎችን ለማስቆጠር ይችልልናል ብዬ ነው፡፡

ስለ ጃንዋሪ ወር እቅዳቸው

‹‹በእኔ አመለካከት የጃንዋሪው የዝውውር መስኮት አዳዲስ ተጨዋቾችን መግዛት ብልህነት ያለው ተግባር ነው፤ ምናልባትም ግን ለቡድናችን የሚጠቅሙ አዳዲስ ተጨዋቾች ዝግጁ ሲሆንልን ፊርማውን ለማግኘት ከፍተኛ የሆነ ጉጉትን የምናሳድር መሆኑን ለማረጋገጥ እወዳለሁ፤ ሆኖም ግን ይህንን ተግባር በመደበኛነት ለመፈፀም ያቀድነው ነገር አለመኖሩን ለማረጋገጥ እወዳለሁ፡፡

The post Sport: ዋይኒ ሩኒ – ወደ ቀድሞ ወርቃማ ዘመኑ ይመለስ ይሆን? appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: 26ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ: አርሰናል የመሪነት ትንቅንቁን ተቀላቀለ ፤ ማን ዩናይትድ ካለፉት 10 ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው 3ን ብቻ ነው

$
0
0

dani

(ዘ-ሐበሻ) 26ኛው ሳምንት የ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ትናንት እና ዛሬ ቀጥሎ ውሏል:: በሳምንቱ የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች ያልተጠበቁ ውጤቶች ተከስተዋል:: ፕሪምየር ሊጉን በ53 ነጥቦች እየመራ የሚገኘው ሌስተር ሲቲ በባከነ ሰዓት በአርሰናል በተቆጠረበት ጎል ቢሸነፍም አሁንም ፕሪምየር ሊጉን እየመራ ይገኛል::

በዳኒ ዌልቤክ የባከነ ሰዓት ጎል ያሸነፈው አርሰናል በ2ኛነት ፕሪምየር ሊጉን እየተከተለ የመሪነት ትንቅንቁን ተቀላቅሏል:: ሌስተር ሲቲ በፕሪምየር ሊጉ አርሰናልን ከ1994 ወዲህ አሸንፎ አያውቅም:: የአርሰናሉ አሰልጣኝ አርሰን ዌንገር ስለዚህ ጨዋታ አስተያየታቸውን ሲሰጡ “ሌስተሮች በመከላከል በኩል ጥሩ ነበሩ:: እስከ እረፍትም 1ለ0 እየተመራ ነበር:: ሌስተሮች በመከላከሉ በኩል ጥሩ ባይሆኑ ኖሮ ብዙ ጎሎችን እናስቆጥር ነበር” ብለዋል::

united

በዘንድሮው ፕሪምየር ሊግ አሰልቺ ጨዋታ እያደረገ ነው እየተባለ በስፖርት ተንታኞች ዘንድ የሚተቸው ማን.ዩናይትድ አሁንም ሽንፈትን አስተናግዷል:: ትናንት በጥቋቁሮቹ ድመቶች 2ለ1 ተሸንፈዋል:: ሰንደርላንድ በፕሪምየር ሊጉ ወራጅ ቀጠና ላይ ያለ ቢሆንም ማን.ዩናይትድን አሸንፈውታል:: ማን.ዩናይትድ ባለፉት 10 የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ውስጥ ማሸነፍ የቻለው 3 ጊዜ ብቻ ሲሆን; 3 ጊዜ አቻ ወጥቶ 4 ጊዜ ተሸንፏል::

በሌሎች ጨዋታዎች ሊቨርፑል አስቶንቭላን ግማሽ ደርዘን ጎል አስቆጥሮበት 6ለ0 አሸንፎታል::
በርንዝማውዝ በስቶክ 3ለ1 ተሸንፏል:: ቸልሲ ኒውካስትልን 5ለ1.. ዌስትብሮም ኤቨርተንን 1ለ0; ዋትፎርድ ክርስታል ፓላስን 2ለ1 እንዲሁም ሳውዛምፕተን ስዋንሳን 1ለ0 ሲያሸንፉ ኖርዊች እና ዌስትሃም 2ለ2 ተለያይተዋል:: ይህ ዜና እየተጻፈ ባለበት ወቅት ማንቸስተር ሲቲ እና ቶተንሃም እየተጫወቱ ነው:: የሆለቱ አሸናፊ ፕሪምየር ሊጎን በ3ኝነት ይመራል::

The post Sport: 26ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ: አርሰናል የመሪነት ትንቅንቁን ተቀላቀለ ፤ ማን ዩናይትድ ካለፉት 10 ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው 3ን ብቻ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: አርሰናል ላይ ዛሬ ሁለቱን ጎል ያገባው ማርከስ ራሽፎርድ ማን ነው?

$
0
0

 

Marcos

Marcos2
በወንደወሰን ጥበቡ | ኢትዮአዲስ ስፖርት

ዛሬ እሁድ ዩናይትድ አርሰናልን በፕሪሚየር ሊጉ ገጥሞ 3ለ2 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ ብዙዎች በጨዋታው ላይ 2 ግቦችን በማስቆጠርና አንድ ደግሞ አመቻችቶ የነበረው ረሽፎርድ ላይ ትኩረታቸውን አድርገው ነበር።

ታዲያ የጨዋታው ኮከብ ይህ ታዳጊ ተጫዋች ማን ነው?
ስም:ማርክስ ራሽፎርድ
የልደት ቀን:ጥቅምት 31፣ 1997 (እ.ኤ.አ)
የትውልድ ስፍራ: ማንቸስተር
የጨዋታ ስፍራው : አጥቂ
ዩናይትድ ተቀላቀለ: ኃምሌ 1፣ 2014

ረሽፎርድ ግሩም በሆነ ሁኔታና ሚዛናዊኑን ጠብቆ መጫወት የሚችል እንዲሁም ኳስን በኃይል አክርሮ መምታት የሚችል ታዳጊ ተጫዋች ነው። ይህ በአሥራዎቹ ዕድሜ ላይ የሚገኝ ታዳጊ በደረጃው አስደናቂ ለውጥ ያደረገ ሲሆን በ2015 የማንችስተር ዩናይትድን የመጀመሪያ ቡድን መቀላቀልም ችሏል።
በ2013/14 የውድድር ዘመን ከሌስተር ሲቲ ጋር በተደረገው የኤፍኤ ወጣቶች ዋንጫ ላይ በድንገት መሰለፍ በመቻሉ የመጀመሪያውን ትልቅ ጨዋታ አድርጓል። በወቅቱ በቦታው ላይ ተሰልፎ ባይጫወትም መጥፎ አቋም ሳያሳይ ወጥቷል።
በ10 ጨዋታዎች ላይ 4 ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ መቻሉና በሚየደርጋቸው የግብ ሙከራ ጥረቶች በታዲጊዎች ማሰልጠኛ ውስጥ የክለቡ መልማዮችን ቀልብ መያዝም ችሏል። ከታቀደለት ጊዜ በፊትም ቀድሞ እንደሄደ እንዲሰማቸው አድርጓል።

ከዩናይትድ ጋር በ2014 በሚልክ ካፕ ጨዋታ ላይ ከተሳተፈ በኋላም ዲሜትሪ ሚሼል በጉዳት ምክኒያት መሰለፍ ባልቻለባቸው ጨዋታዎች ላይ የዩናይትድ ታዳጊ ቡድን ዋና አጥቂ ሆነ። በእነዚህ ጊዜያትም የመሃል ለመሃል የፊት ተጫዋችነት ሚናን በሚገባ ልምድ ቀስሟል። በ25 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 13 ግቦችን ከመረብ በማዋሃድ የኮክብነት ተስፋ ያለው ተጫዋች መሆኑንም አሳይቷል። በወጣቶች የኤፍኤው ዋንጫ ላይ በቶተንሃም ላይ ያስቆጠረው ድንቅ ቅጣት ምት ተጫዋቹ በቆሙ ኳሶች ላይ ያለውን ብቃት ማሳየት የቻለም ነበር።

arsenal
ከ18 ዓመት ዕድሜ በታች ቡድን ውስጥ በመደበኛነት ግብ ማስቆጠሩን ቀጥሎበትም በዋርን ጆይሱ ከ21 ዓመት በታች የዩናይትድ ቡድን ውስጥ የመጫወት ዕድል አግኝቷል።

ይህን ቡድንም በአውሮፓ ህብረት የእግር ኳስ ማህበር የወጣቶች ሊግ መድረክ ላይ ከኒኪ በት የአምበልነት የክርን ማዕረጉን ተቀብሎ ቡድኑን በአምበልነትና በፊት ተጫዋችነት መርቷል። ታታሪው አጥቂ ከ21 ዓመት በታች ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ መሰለፍ የቻለው ቡድኑ ሌስተርን 6ለ1 በረታበት ታህሳስ ወር አጋማሽ ላይ ነበር። እንዲሁም በኤፍኤው የወጣቶች ዋንጫ ውድድር ላይ ጉልህ የሆነ ቁልፍ ሚናም ነበረው።

The post Sport: አርሰናል ላይ ዛሬ ሁለቱን ጎል ያገባው ማርከስ ራሽፎርድ ማን ነው? appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ናቾ ሞንሪያል –የመድፈኞቹ እጅግ ተፈቃሪው ተጨዋች

$
0
0

 

arsenal Nocho

ስፔናዊው ግራ ተመላላሽ ናቾ ሞንሪል በጃንዋሪው 2013 በአርሰናሉ አርሴን ቬንገር ከማላጋ ክለብ የተገዛው በቡድናቸው የግራ ተመላላሽ ሚና የመጀመሪያው ተመራጭ ለነበረው ኬራን ጊብስ ትክክለኛው ሽፋንን ለመስጠት የሚችልበት ብቃትን ተላብሷል በሚል ታምኖበት ነበር፡፡ በአርሰናል የፈረመበት የመጀመሪያው ዓመትን ያጠናቀቀው ከእንግሊዝ ፉትቦል የጨዋታ ስታይል ጋር በአግባቡ ለመላመድ ጥረትን ለማድረግ ተገድቦ ቢሆንም ቀስ በቀስ አርሰናል የመጀመሪያ ተመራጭ ተጨዋች መሆን ችሏል፡፡

የሞንሪል የአርሰናል መፈረምን ተከትሎም የሰሜን ለንደኑ ክለብ ደጋፊዎች በድፍን ዘጠኝ ዓመታት የዘለቀው የዋንጫ ሽልማት ጉጉታቸውን ለመቅረፍ ያለፉት ሁለት ተከታታይ ዓመታት የኤፍ.ኤ ካፕ ድልን ተቀዳጅቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት አርሰናል የዘንድሮው ሲዝንን ከ3ኛ ጊዜ በተከታታይ የኤፍ.ኤ.ካፕ የዋንጫ ድልን በመቀዳጀት በውድድሩ ታሪክ ብቸኛው ክለብ የመሆን ታሪክን ለመስራት ከመጓጓት አልፎ ከ2004 የዘለቀው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮንነት ክብር ናፍቆቱን የመቅረፍ አላማን እንዲይዝ በዋነኝነት የሚጠቀስ ምክንያት የሆነ ታላቅ ፐርፎርማንስን ለማበርከት ላይ ከሚገኙለት ተጨዋቾችም ውስጥ አንዱ ናቾ ሞንሪል ነው፡፡

ምክንያቱም በዘንድሮው ሲዝን በእያንዳንዱ የአርሰናል ግጥሚያዎች ላይ በመደበኛ ቋሚ ተሰላፊነት በመጫወት የቡድኑ የግራ መስመር እጅግ ጠንካራ ሆኖ እንዲዘልቅ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ አስተዋፅኦን ለማበርከት ችሏል፡፡ ይህንን ከግንዛቤ በማስገባትም አርሴን ቬንገር ሰሞኑን ለሞንሪል ከክለባቸው ጋር ለተጨማሪ ዓመታት የሚዘልቅበትን አዲስ ኮንትራት ማራዘሚያ ውልን ፈቅደውለታል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ፈረንሳዊው አሰልጣኝ በያዝነው ሳምንት ውስጥ በሰነዘሩት አስተያየትም ናቾ ሞንሪልን በስኳዳቸው በሚያገኙት በእያንዳንዱ የቡድናቸው ተጨዋቾች በከፍተኛ ደረጃ የሚፈቀር ተጨዋች ነው በማለት ገልፀውታል፡፡

Nocho2

ሞንሪል በአሁኑ ወቅት በስኳዳችን ከሚገኙትና ከቡድናችን እጅግ ከፍተኛ ወሳኝነት ካላቸው ተጨዋቾች ውስጥ አንዱ መሆኑን መጠራጠር በፍፁም አያሻም፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ያካበተው ሰፊ ልምድን መሰረት በማድረግ እያንዳንዱ የቡድናችን ተጨዋቾች እንደ ትልቅ አርአያቸው የሚቆጥሩና በከፍተኛ ደረጃ የሚፈቀሩት ተጨዋች መሆኑን ለማረጋገጥ እወዳለሁ›› በማለት በስፔናዊው ግራ ተመላላሽ ዙሪያ መግለጫቸውን መስጠት የጀመሩት አርሴን ቬንገር በመቀጠልም ‹‹በቡድናችን በዘንድሮው ሲዝን በግራ መስመሩ ካለፉት ዓመታት በብዙ መልኩ የተሻለ የተረጋጋ ጥሩ አቋም እንዲኖው ግንባር ቀደሙን አስተዋፅኦን ያበረከተው በመሆኑ የተፈቀደለት አዲስ የኮንትራት ማራዘሚያን ውል በትክክልም በሚመጥነው መሆኑን አምናለሁ›› የሚል አስተያየታቸውን አክለዋል፡፡

ሞንሪል በእስካሁኑ ሲዝን የያዘው የማይዋዥቅ ታላቅ ፐርፎርማንስን ለማበርከት አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ከአርሰናል መደበኛ ቋሚ ተሰላፊዎች ውስጥ የያዛቸው ብቃት አስፈላጊው ከበሬታን ያላገኘለት ተጨዋች ነው በማለት ላይ ናቸው፡፡ በዚህ አመለካከት ዙሪያ አርሴን ቬንገር አስተያየታቸውን የሰነዘሩት ‹‹እኔ እስከሚገባኝ ድረስ የሌሎቹ ተቀናቃኞቻችን ክለቦች አባላትም የሞንሪል የተዋጣለት የግራ መስመር ተመላላሽ ሚና ባለቤት መሆንን በአግባ የተረዱበት የውድድር ዘመን ላይ እንገኛለን፡፡ ማንኛውም አስተያየት ሰጪ ቢሆን ሞንሪልን ፍፁም እንከን የማይወጣለት ታላቅ ፐርፎርማንስን ለማበርከት ባህሉ ያደረገበት የውድድር ዘመንን በማሳለፍ ላይ መሆኑን ሊመሰክርለት ይችላል፡፡ ከግራ ተመላላሽ ሚና ባሻገር አስፈላጊ በሚሆንበት ወቅት በመሀል ተከላካይ ክፍል በመሰለፍ ለቡድናችን ተጨማሪ ትልቅ ኃላፊነትን የሚፈፅምልን ተጨዋች ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ በእያንዳንዱ ግጥሚያ የሚሰጠውን ኃላፊነትን ለመፈፀም 100 ፐርሰንት ጥረትን የማድረግ ባህሉ ለሌሎች የቡድናችን ተጨዋቾች በትልቅ አርአያነት የሚጠቀስለት ባህሉ ነው፡፡

 

በአቡኑ ወቅት ቡድናችን በሞንሪልና በኬራን ጊብስ አማካይነት ሁለት ወርልድ ክላስ የግራ ተመላላሽ ሚና ባለቤቶችን መያዙም እድለኛ እንደሀነ ያህል ይሰማኛል፡፡ ምክንያቱም በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሚገኙት አብዛኛዎቹ ክለቦች ከዚህ ቦታ ላይ መሰረታዊና ያለው የመሳሳት ችግር በግልፅ በመታየት ላይ ነው፡፡ ከዚህ መልካም አጋጣሚያችን በአግባቡ ተጠቃሚ በመሆን የዘንድሮው ሲዝንን በምንሳተፍባቸው ውድድሮች ሁሉ መልካም ውጤቶችን በማስመዝገብ ለማጠናቀቅ የማናልምበት ምክንያት አይኖርም ብለዋል፡፡

ስፔናዊው ኢንተርናሽናል ግራ ተመላላሽ በበኩሉ አርሰናል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጠንካራ አቋምን በመያዝ በአሁኑ ወቅት የፕሪሚየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥን በመምራት ላይ ካለው ሊስተር ሲቲ የሁለት ነጥቦች ልዩነት በማነስ የሻምፒዮንነት ፉክክሩ ዋነኛ ተዋናይ የሆነው አብዛኛዎቹ ተጨዋቾች ሳይበታተኑ አብረው ብዛት ባላቸው ግጥሚያዎች ላይ የመሰለፍ እድልን ማግኘታቸው መሆኑን ያመነበት መግለጫን ከትናንት በስቲያ ሰጥቷል፡፡

አርሴን ቬንገር ባለፉት ሁለት ተከታታይ የዝውውር መስኮቶች ከአርሰናል አዲስ ያስፈረሟቸው ተጨዋቾች ፒተር ቺክና መሐመድ አልኔኒይ ብቻ መሆናቸውን በማስገንዘብ ሞንሪል መግለጫውን የሰጠው ‹‹በእኔ አመለካከት በስኳዳችን የሚገኙት አብዛኛዎቹ ተጨዋቾች ከሁለትና ከሶስት ዓመታት በላይ በበርካታ ግጥሚያዎች ላይ አብረው የመሰለፍ እድልን ያገኙ መሆናቸው በመሃላቸው እጅግ ተደናቂ ህብረት እንዲፈጠር የበኩሉን ትልቅ አስተዋፅኦን አበርክተውልኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመሃላችን ያለው ህብረትም እጅግ ጠንካራ ነው፡፡ በሜዳ ላይ ብቻ ሳይሆን ከሜዳው ውጪም አብዛኛውን ጊዜያችንን አብረን ማሳለፋችን በመሀላችን ያለው የእርስ በርስ መፈቃቀር ከፍተኛነትን የማያንፀባርቅ ነው፡፡

Arsenal v Stoke City - Barclays Premier League

ለአንድ ቡድን የዋንጫ ሽልማቶችን ለማግኘት እንዲችል ትልቅ አስተዋፅኦን የሚያበረክትለት ጉዳይ ደግሞ በቡድኑ ካምፕ የሚኖረው ህብረት ያማረ መሆን ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ይህንን ከፍተኛ ወሳኝነት ያለው ክራይቴሪያን በተሟላ ሁኔታ ለመያዝ ችለናል የሚል እምነት አለኝ›› በማለት ነው፡፡ የአርሰናሉ አሰልጣኝ አርሴን ቬንገር በእያንዳንዱ የዝውውር መስኮት ከአንድ ወይም ከሁለት የማይበልጡ አዲስ ተጨዋቾችን ማስፈረምን በቅርቡ ዓመታት ውስጥ የተለመደ ባህላቸው ማድረጋቸው የበኩሉን ትልቅ አስተዋፅኦን እንዳበረከተላቸው በማመን ሞንሪል በመቀጠል የሰጠው መግለጫ ‹‹…አርሰናል በ11 ተጨዋቾች ክለብ በቻ አይደለም በዋናው ቡድናችን ስኳድ የሚገኙት ሁለት 24 ተጨዋቾች አንዳንድ ህብረትን በመፍጠር ተደናቂ ስኬቶችን ለማስመዝገብ የተቻላቸውን ሁሉ ጥረትን የሚያደርጉበት ህብረቱና አጠቃላዩ ቅንጅቱ ያማረ ክለብ ነው፡፡ ለዚህ የረዳን ደግሞ በእያንዳንዱ የዝውውር መስኮት ከአንድ የማይበልጥ አዲስ ተጨዋቾችን ማስፈረማችንን የተለመደ ባህላችንን ማድረጋችን መሆኑን አምናለሁ፡፡ ለዚህ ክለብ ከመጣሁበት ጊዜ አንስቶም በስኳዳችን ያለው ህብረትን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ ለመምጣት ምስክርነቱን መስጠት እችላለሁ፡፡ አብዛኛዎቹ የቡድናችን ተሰላፊዎች ከሁለት ዓመታት በላይ አብረን የመጫወት እድልን በማግኘታችንም በመሃላችን ያለው አጠቃላዩ ቅንጅትና የጨዋታ እንቅስቃሴ መናበብ ይበልጥ እያማረ ሊሄድልን ይችላል›› በማለት ነው፡፡

 

The post Sport: ናቾ ሞንሪያል – የመድፈኞቹ እጅግ ተፈቃሪው ተጨዋች appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 419 articles
Browse latest View live