(ዘ-ሐበሻ) አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በሪዮ ኦሎምፒክ እጆቹን ወደላይ አጣምሮ የታሰርናል ምልክትን አሳይቶ ገዳዩን የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት በተቃወመ በሳምንቱ ሌላው ጀግና አትሌት ኢብሳ እጅጉም ታሪክ በመስራት ዛሬ በካናዳ የታረናል ምልክት በማሳየት ተቃውሞን ገለጸ::
አትሌት ኢብሳ እጅጉ በካናዳዋ ኪውቤክ ከተማ በተደረገው የማራቶን ውድድርን 2:30:40 በመግባት ያሸነፈ ሲሆን የውድድሩን ሪቫን በጥሶ ሊገባ ሲል እጆቹን ወዳላይ በማንሳትና በማጣመር በሕወሓት መንግስት ኢትዮጵያ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የሰብ አዊ መብት ጥሰትና ግድያን አውግዟል::
የአትሌት ኢብሳን ዜና በርካታ የውጭ ሚድያዎች ከአትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ጋር በማያያዝ በሳምንቱ ታሪክን ደገመ እያሉ እየዘገቡት ይገኛሉ::