ለጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ መታሰቢያ በጃፖን ካሳማ ከተማ ከነገ በስቲያ የግማሽ ማራቶን ውድድር ይካሄዳል፡፡ በውድድሩ ላይ ለመካፈልም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ልኡካን ቡድን በስፍራው መገኘታቸውን ፌዴሬሽኑ በድረገጹ አስነብቧል፡፡ የፌዴሬሽኑን ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ እና የሻምበል አበበ ቢቂላን ልጅ አቶ የትናየት አበበን ያካተተው ልኡክም በቶኪዮ ኦሊምፒክና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ገንቢ ውይይት ማካሄዱ ታውቋል። በብርሃን ፈይሳ ፎቶ ፦ ከማህበራዊ ድረ ገጽ (ኢ.ፕ.ድ)
The post ለአበበ ቢቂላ መታሰቢያ የግማሽ ማራቶን ውድድር ሊካሄድ ነው appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.